Sunday, May 10, 2015

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤15 ክፍል ስምንት

በስም አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

ከሐሰተኛው ‹‹መምህር›› ተጠበቁ!

የተከበራችሁ አንባብያን!

“የበግ ለምድ ለብሰው ከሚመጡባችሁ በውስጣቸው ግን ነጣቂዎች ተኩላዎች ከሆኑ ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡ ከፍሬያቸው ታውቋቸዋላችሁ፡፡ ከእሾህ ውይን ክኩርንችትስ በለስ ይለቀማልን ? እንዲሁ መልካም ዛፍ ሁሉ መልካም ፍሬ ያደርጋል፡፡ክፉም ዛፍ ክፉ ፍሬ ያደርጋል፡፡”ማቴ.7፤15-18 የሚለውን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ክፍለ ትምህርት መነሻ ርዕስ አድርገን ባቀረብነው ተከታታይ ጽሁፍ ፤ መናፍቃን /ተሐድሶ ነን ባዮች/ በውስጥም በውጭም ሆነው በኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ሃይማኖታችን ላይ እየዘሩ ያሉትን የኑፋቄ እንክርዳድ በተመለከተ እያንዳንዱ ምዕመን ቢያንስ እራሱን ከስህተት ትምህርታቸው ለመጠበቅ የሚያስችለውን ያህል መጠነኛ ገንዛቤ ለማስጨበጥ ሞክረናል፡፡ወደፊትም እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ እንቀጥላለን፡፡

ለዛሬው ስለ አንድ የውስጥ መናፍቅ የኑፋቄ ሥራ እንመለከታለን፡፡

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤15 ክፍል ሰባት

በመዝሙር ስም ዘፈን! እስከ መቼ ?

የተከበራችሁ የዚህ ድረ ገጽ ታዳሚዎች! እንደምን ሰነበታችሁ?

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” በሚለው ዋና ርዕሳችን ሥር ‹‹በመዝሙር ስም ዘፈን! እስከ መቼ?›› በሚለው ንዑስ ርዕስ የመጀመሪያውን ክፍል መግቢያውን ተመልክተን በይቀጥላል አቆይተነው እንደነበር ይታወሳል፡፡ከዚህ በመቀጠል ደግሞ በ‹‹መዝሙር›› ስም ወደ ቤተ ክርስቲያናችን ሠርጎ ስለገባው ስህተት ትክክለኛ ግንዛቤ እንዲኖረን ከብዙው በጥቂቱ እንመለከታለን፡፡ 
እነዚህ የተለያዩ የጥፋት መልእክተኞችና እኩይ ሥራቸው ቁጥራቸው ከመብዛቱ የተነሳ እያንዳንዳቸውን በዝርዝር ለማየት አስቸጋሪ በመሆኑ ብዙዎቹን ችግሮች አንድ እያልን በሦስት ዋና ዋና ክፍሎች ከፍለን እናያቸዋለን፡፡ምንም እንኳን ከሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን የወጡ እነዚህን ‹‹መዝሙሮች›› ‹‹መዝሙር›› ብለን መጥራት ባይገባንም፤ለጊዜው የምንግባባው በዚሁ ቃል በመሆኑ እኛም ይህንኑ ቃል ተጠቅመን ጽሁፋችንን እንቀጥላለን፡፡