‹‹ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ›› በሚለው ዐቢይ ርዕስ ሥር ከክፍል አንድ እስከ ዘጠኝ ባስነበብነው ጽሁፍ የዘመናችን የቤተ ክርስቲያናችን ትልቅ ፈተና የሆኑትን እራሳቸውን ‹‹ተሐድሶ ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ››ብለው የሚጠሩትን የበግ ለምድ የለበሱ ተኩላዎችን የጥፋት ተልእኮ ለማሳየት ሞክረናል፡፡የእኩይ ሥራቸው ፍሬዎች ከሆኑት መጻሕፍቶቻቸውም መካከል ‹‹የአዲሰ ኪዳን መካከለኛ» የተባለው መጽሐፍ በመጽሐፍ ቅዱስ ሲመዘን ቀሎ የተገኘ /ከፍሬው ገለባ/ መሆኑንም መጽሐፍ ቅዱስን ምስክር አድርገን አሳይተናል፡፡እንዲሁም በክፍል አስር "ቢኒ ዘልደታ" የተባሉት ወንድማችን ያዘጋጁትን ወቅታዊ የተሐድሶ መናፍቃን እንቅስቃሴ የሚገልጽ ጽሁፋቸውን አስነብበናችኋል፡፡
ከዚህ በመቀጠል ደግሞ ስለዚሁ ወቅታዊና ፈታኝ ስለሆነው የኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን ችግር (የውስጥና የውጪ መናፍቃን) ጉዳይ ማህበረ ቅዱሳን በድረ-ገጹ (www.eotcmk.org) " የተሐድሶን ምንነት ሳታውቁ፣ ስለ ተሐድሶዎች ማንነት አትጠይቁ!! " በሚል ርዕስ ያሰፈረውን በማስረጃ የተደገፈ ዘገባ ምንም ሳንጨምርና ሳንቀንስ አቅርበነዋል፡፡
መልካም ንባብ!