Sunday, December 13, 2015

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤15 ክፍል አስራ ሦስት

ከቁጥር አስራ ሁለት የቀጠለ

የተወደዳችሁ አንባብያን!
እንደምን ሰነበታችሁ ?

‹‹ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ›› በሚለው ዐቢይ ርዕስ ሥር፤ በክፍል አስራ አንድና አስራ ሁለት ላይ ወቅታዊ የሆነውን የኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን የውስጥና የውጪ መናፍቃን/ተሐድሶዎች/ ችግር በማስመልከት ማህበረ ቅዱሳን በድረ-ገጹ (www.eotcmk.org) ያቀረበውን ዘገባ ተመልክታችሁ ጥሩ ግንዛቤ እንዳገኛችሁ በመገመት፤በመቀጠል ደግሞ "የተሐድሶ መረብ አድማስና የትኩረት አቅጣጫ" "ንቁ ሳይሆን ተናነቁ" "መንፈሳዊ ኮሌጆችና ደቀ መዛሙርቱ ምንና ምን ናቸው?" በሚሉት ርዕሶች ከማህበረ ቅዱሳን ያገኘነውን በማስረጃ የተደገፈ ዘገባ እነሆ ብለናል፡፡ 

ማስገንዘቢያ፤

የተከበራችሁ አንባብያን የቤተ ክርስቲያን አምላክ ልዑል እግዚአብሔር አስቀድሞ በቅዱስ ወንጌል እንዲሁም በየጊዜው ደግሞ በተለያየ መንገድ የሚናገረን እራሳችንንም ሆነ ሌላውን ከስህተት ጎዳና እንድንጠብቅ ነው፡፡ስለሆነም እያንዳንዳችን የቤ/ክ ልጆች "ከእኔ ምን ይጠበቃል?"ብለን በመጠየቅ የቤ/ክ እምነት፣ሥርዓትና ትውፊት ከአባቶቻችን በተረከብነው መሠረት እንዲቀጥል ለማድረግ በጾምና በጸሎት ከመታገዝ ጋር አቅማችን የሚችለውን ሁሉ በማድረግ መንፈሳዊ ግዴታችንን እንድንወጣ በቅዱሳን አምላክ በልዑል እግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን፡፡

መልካም ንባብ!

Thursday, December 3, 2015

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤15 ክፍል አስራ ሁለት

የተወደዳችሁ አንባብያን!
እንደምን ሰነበታችሁ ?
     ‹‹ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ›› በሚለው ዐቢይ ርዕስ በክፍል አስራ አንድ ላይ ወቅታዊ የሆነውን የኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን  (የውስጥና የውጪ መናፍቃን) ችግር በማስመልከት ማህበረ ቅዱሳን በድረ-ገጹ (www.eotcmk.org) " የተሐድሶን ምንነት ሳታውቁ፣ ስለ ተሐድሶዎች ማንነት አትጠይቁ!! " በሚል ርዕስ ያሰፈረውን በማስረጃ የተደገፈ ዘገባ አንብባችሁ ጥሩ ግንዛቤ እንዳገኛችሁ እናምናለን፡፡

     ከዚህ በመቀጠል ደግሞ እነዚሁ ሃይማኖት እናድሳለን ባዮች በቤተ ክርስቲያናችን ላይ እያደረሱ ያለውን ችግር ማህበረ ቅዱሳን በድረ-ገጹ (www.eotcmk.org) በተከታታይ ያቀረበውን ቀጣይ ጽሁፍ ባለበት ሁኔታ /እንዳለ/ አቅርበነዋል፡፡
ማስገንዘቢያ፤
     የተከበራችሁ አንባብያን የቤተ ክርስቲያን አምላክ አስቀድሞ በወንጌል እንዲሁም በየጊዜው ደግሞ በአንድም በሌላም መንገድ የሚናገረን እራሳችንንም ሆነ ሌላውን ከስህተት ጎዳና እንድንጠብቅ ነው፡፡ስለሆነም እያንዳንዳችን "ከእኔ ምን ይጠበቃል?"ብለን በመጠየቅ የቤ/ክ እምነት፣ሥርዓትና ትውፊት ከአባቶቻችን በተረከብነው መሠረት እንዲቀጥል ለማድረግ በጾምና በጸሎት ከመታገዝ ጋር አቅማችን የሚችለውን ሁሉ በማድረግ መንፈሳዊ ግዴታችንን እንድንወጣ በቅዱሳን አምላክ በልዑል እግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን፡፡
መልካም ንባብ!