Sunday, February 5, 2017

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤16 ክፍል ሃያ ስምንት

ከክፍል ሃያ ሰባት የቀጠለ

     የተከበራችሁ  የዚች ጦማር ተከታታዮች ምእመናን! እንደምን ሰነበታችሁ? ለዚች ዕለትና ለዚች ሰዓት ያደረሰን ልዑል እግዚአብሔር ከዓለም ዳርቻ እስከ ዓለም ዳርቻ የተመሰገነ ይሁን፡፡በአገልግሎት መብዛት ምክንያት ወቅታዊ መልእክቶችን ከማስተላለፍ ስለዘገየን አስቀድመን ይቅርታ እንጠይቃለን፡፡
     ሐዋርያው ቅ/ጳውሎስ በሮሜ መልእክቱ ምዕ.፲፪ ቁጥር ፱  “ክፉውን ነገር ተጸየፉት፤ከበጎ ነገር ጋር ተባበሩ” ብሎ ባስተማረን መሠረት፤ዓላማችን አንድ እስከሆነ ድረስ፤የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ሃይማኖትና ሥርዓት ጠብቀው የሚያስተምሩትን የተለያዩ መምህራንን ትምህርቶች፤በዚች የመወያያ ጦማር ላይ እንድታነቡ ስናደርግ እንደነበረው፤በዚች ክፍል የምናስነብባችሁ ዲያቆን ብርሃኑ አድማስ “ሠለስቱ ደቂቅን ከእሳት ያዳናቸው መልአክ ማን ነው?”በሚል ርዕስ ያስተላለፉትን እጅግ ተቃሚ ትምህርት በድረ ገጻቸው በጊዜው ማንበብ ላልቻላችሁ ምእመናን አቅርበንላችኋል፡፡ሙሉው መልእክት የዲያቆን ብርሃኑ አድማስ ነው፤ጽሁፉ ለንባብ እንዲመች ከማድረግ በስተቀር የራሳችንን ሃሳብ አልጨመርንም፡፡
መልካም ንባብ!