Saturday, February 24, 2018

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤16 ክፍል ሰላሳ ዘጠኝ

ከክፍል ሰላሳ ስምንት የቀጠለ፦

የተከበራችሁ የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ልጆች!

እንኳን ለእናታችን ለወላዲተ አምላክ ለቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ የቃል ኪዳን በዓል አደረሳችሁ አደረሰን፡፡

     ከዚህ በመቀጠል ስለ እመቤታችን ክብር ተናግረው የማይጠግቡት፤በተለይም ውዳሴዋንና ቅዳሴዋን በመተርጎምና የዘመኑን ቴክኖሎጂ በመጠቀም ሁላችንም በየቤታችን እንድንሰማውና እንድንማርበት እንድንቀደስበትም በሲዲ አዘጋጅተው ያበረከቱልን መምህራችን ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን ደምፀ፤ የእመቤታችንን የኪዳነ ምሕረት በዓል በማስመልከት በማሕበራዊ ድረ-ገጽ ያስተላለፉትን ትምህርት ከዚህ ቀጥሎ አቅርበንላችኋል፡፡

Sunday, February 11, 2018

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤16 ክፍል ሰላሳ ስምንት

ከክፍል ሰላሳ ሰባት የቀጠለ፦
     የተወደዳችሁ አንባብያን! እንኳን የካቲት አምስት ቀን 2010 ዓ.ም ለምንጀምረው ዐቢይ ጾም  በሰላምና በጤና አደረሳችሁ አደረሰን፡፡
     ከዚህ በመቀጠል ስለ ዐቢይ ጾም መጠነኛ ግንዛቤ የምናገኝበት ትምህርት፤እንዲሁም በዐቢይ ጾም ውስጥ በሚውሉት ስምንት ሰንበታት  /እሑዶች/ በቅዳሴ ጊዜ የሚነበቡትን ምንባባት በተመለከተ በዝርዝር አቅርበንላችኋልና በጥሞና እንድትከታተሉት እንጋብዛለን፡፡