Sunday, January 25, 2015

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤15 ክፍል ሦስት

ከቁጥር ሁለት የቀጠለ
የተወደዳችሁ አንባብያን!
     ቀደም ብለን ባስነበብናችሁ ሁለት ክፍሎች የቤተ ክርስቲያን ሳይሆኑ በተለያየ መንገድ የቤተ ክርስቲያን መስለው ስለሚያሳስቱ መናፍቃን የተወሰነ ግንዛቤ ለማሰጨበጥ ሞክረናል፡፡ሆኖም ዋና ዋናውን ጥፋታቸውን ለማመላከት ያህል ነው እንጂ የማሳሳቻ ስልታቸው ይህ ብቻ ነው ማለት አይደለም ፡፡ከሚናገሩትና ከሚጽፉት በተጨማሪ ዲያቆን ፣ካህን፣መነኩሴ፣ሰባኬ ወንጌል፣ወ...መስለው ለማሳሳት ካባውን፣ቆቡን፣መስቀሉንና ቀሚሱን ለብሰው ከበሮውን፣ ጸናጽሉን፣መቋሚያውንና የመሳሰለውን የቤ/ ንዋያተ ቅድሳት ይዘው በተለያዩ የሕዝብ መገናኛዎች ሳይቀር /የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ጨምሮ/ የሐሰት ትምህርታቸውን በቤተ ክርስቲያናችን ስም ያስተላልፋሉ፡፡እኛ የተዋህዶ ልጆች የእኛና የእነሱ የሆነውን ለመለየት ነቅተንና ተግተን እራሳችንንም ሆነ ቤተ ክርስቲያናችንን ከስህተቱ መጠበቅ ይኖርብናል፡፡

ከፍሬያቸው ታውቋቸዋላቸሁ

     ከላይ በመግቢያችን ላይ በጠቀስነው ወንጌል በጎችንና ተኩላዎችን መለየት የሚንችለው በሚሰሩት ሥራ እንደሆነ ተመልክተናል፡፡ከዚህ በመቀጠል ከእኩይ ሥራቸው አንዱ የሆነውንና በእነሱው ከሚዘጋጁት የተለያዩ መጽሐፎቻቸው አንዱ የሆነውንየአዲሰ ኪዳን መካከለኛየተባለውን መጽሐፋቸውን እኛ ደግሞ “‹‹የአዲሰ ኪዳን መካከለኛ» በመጽሐፍ ቅዱስ ሲመዘን በሚል ርዕስ እናየዋለን፡፡

Monday, January 19, 2015

“ ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤15“ ክፍል ሁለት

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

ከቁጥር አንድ የቀጠለ
ተከበራችሁ አንባብያን!
     “ ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡”በሚለው ርዕስ እንደ መግቢያ የሆነውን ክፍል አንድን ተመልክተን በይቀጥላል አቆይተነው እንደነበር የታወሳል፡፡ ስለሆነም በገባነው ቃል መሰረት ወደ ዝርዝር ጉዳዩ ከመግባታችን በፊት ነገር ከሥሩ ውሃ ከጥሩ ነውና በአሁኑ ጊዜ እራሳቸውን  “ተሐድሶ ዘኦርቶዶክስ ተዋህዶ” ብለው ስለሚጠሩት ክፍሎች  ወቅታዊ ግንዛቤ መጨበጥ ይኖሮብናል፡፡
     እነዚህ ክፍሎች ቀደም ባሉት በ1980ዎቹ ዓመታት እንዲህ እንደ አሁኑ ሳይደራጁ ማለትም ገና በጽዋ ማህበር ደረጃ ይሰባሰቡ በነበረ ጊዜ ቤተ ክርስቲያንን የማፍረስ ዓላማቸውን እንዲህ በለው ገልጸውት ነበር፡፡“ አስቀድሞ የተመሠረተው መሠረት (የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት) በአንድ ጊዜና በቀላሉ ተገርስሶ ሊወድቅ አይችልም፡፡እኛ ሥርዓቱን ለይምሰል እየፈጸምን ውስጥ ውስጡን የእኛን እውነት ስናስተምር ያ የቀድሞው መሰረት ቀስ በቀስ እየተሸረሸረ ሲወድቅ ያን ጊዜ የኛ መሰረት በዚያ ላይ ይመሰረታል፡፡”በማለት ነበር ገና ከጅምሩ ከሐዋርያው ከቅዱስ ጳውሎስ መልእክት ጋር የተጣሉት፡፡ እንጠቅሳለን ፦“በሐዋርያትና በነቢያት መሠረት ላይ ታንጻችኋል የማዕዘኑም ራስ ድንጋይ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፡፡ኤፌ.2፤20-21 እንዲሁም“ ከተመሰረተው በቀር ማንም ሌላ መሠረት ሊመሰርት አይችልምና ፤እርሱም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡” 2ኛ ቆሮ.3፤11 
  ቅ/ጳውሎስም ይህንን መልእክት የጻፈው ከራሱ ልብ አመንጭቶ ሳይሆን የዓለም መድኃኒት ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተናገረውንና ወንጌላዊው ማቴዎስ በወንጌሉ ምዕ.16 ቁ.16-20 እንዲህ ብሎ የመዘገበውን መሠረት አድርጎ ነው፡፡ “ስምዖን ጴጥሮስም መልሶ አንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ ” አለ፡፡ጌታችንም መልሶ…“.በዚችም ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሰራለሁ፤ የገሃነም ደጆችም አይችሉአትም፡፡…” በማለት

Tuesday, January 13, 2015

“ ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤15“ ክፍል አንድ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን::

    “የበግ ለምድ ለብሰው ከሚመጡባችሁ በውስጣቸው ግን ነጣቂዎች ተኩላዎች ከሆኑ ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡ ከፍሬያቸው ታውቋቸዋላችሁ፡፡ ከእሾህ ውይን ክኩርንችትስ በለስ ይለቀማልን ? እንዲሁ መልካም ዛፍ ሁሉ መልካም ፍሬ ያደርጋል፡፡ክፉም ዛፍ ክፉ ፍሬ ያደርጋል፡፡ማቴ.715-18           
      ይህንን ኃይለ ቃል የተናገረው ጌታችን አምላካችንና መድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ በዚህ ክፍለ ትምህርት ጌታችን ተጠበቁ ፣ተጠንቀቁ ብሎ ያስተማረን  እውነተኞቹን በጎች መስለው በበጎቹ መንጋ ውስጥ የተቀላቀሉትን ተኩላዎች መለየት እንድንችል ሲሆን የማንነታቸው መለያው የስራ ፍሬያቸው እንደሆነ ገልጾልናል፡፡ስለዚህ የሰውን ልቡና መርምሮ የሚያውቀው ልዑል እግዚአብሔር ብቻ ሲሆን እኛ ግን ማንንም ሰው የሚናገረውንና የሚሰራውን አይተንና ሰምተን ምንነቱን ማወቅ እንችላለን ማለት ነው፡፡ስለሆነም በዚህ ሐሰት በነገሰበት፤እውነትና እውነተኛ በጠፋበት አሰጨናቂ ዘመን መናፍቁን ከእውነተኛው አማኝ ለይተን እራሳችንንና ሌላውንም ከክህደትና ከኑፋቄ መጠበቅ ፤ከአባቶቻችን የተረከብናትን በነቢያትና በሐዋርያት መሠረት ላይ የታነጸችውን ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ሃይማኖታችን እምነቷ፣ሥርዓቷና ትውፊቷ ሳይፋለስ ለቀጣዩ ትውልድ እንድትተላለፍ ማድረግ የሁላችንም መንፈሳዊ ግዴታ ስለሆነ ከማንኛውም ጊዜ በላይ በሃይማኖትም ሆነ በምግባር ጠንክረን መገኘት ያለብን ጊዜው አሁን እንደሆን ማስተዋል ይገባናል፡፡
     ሁላችንም እንደምናየውና እንደምናውቀው በዓለማችን ውስጥ አንድ ዓይነት መጽሐፍ ቅዱስ ይዘው እንደየራሳቸው ስሜት እየተረጎሙ የየራሳቸውን የእምነት ድርጅት አቋቁመው