Saturday, May 21, 2016

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤16 ክፍል ሃያ

የተወደዳችሁ አንባብያን!
እንደምን ሰነበታችሁ ?
በክፍል አስራ ዘጠኝ ጽሁፋችን "ተሐድሶ ዘኦርቶዶክስ የእምነት መግለጫ" በመጽሐፍ ቅዱስ ሲመዘን! በሚል ርዕስ ጀምረን በይቀጥላል እንዳቆየነው ይታወሳል፡፡ ክፉውን ነገር እንድንጸየፍ ከበጎ ነገር ጋር እንድንተባበር ከቅዱሳት መጻሕፍት በተማርነው መሠረት ‹‹ቲጂ የተዋህዶ ልጅ ተዋህዶ››የተባለች እህታችን በface book ያስተላለፈችው ትምህርት የእኛም መልእክት ስለሆነ ሳንጨምርና ሳንቀንስ እንድታነቡት እንጋብዛለን፡፡

Sunday, May 1, 2016

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤16 ክፍል አስራ ዘጠኝ

   “ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡ማቴ.716 ክፍል አስራ ዘጠኝ
 "ተሐድሶ ዘኦርቶዶክስ የእምነት መግለጫ" በመጽሐፍ ቅዱስ ሲመዘን!
ከክፍል አስራ ስምንት የቀጠለ
የተወደዳችሁ አንባብያን!
እንደምን ሰነበታችሁ ?
‹‹ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ›› በሚለው ዐቢይ ርዕስ ሥር ከክፍል አንድ እስከ ዘጠኝ ባስነበብነው ጽሁፍ፤የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያናችን ትልቅ ፈተና የሆኑትን እራሳቸውን ‹‹ተሐድሶ ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ››ብለው የሚጠሩትን የበግ ለምድ የለበሱ ተኩላዎችን የጥፋት ተልእኮ ለማሳየት ሞክረናል፡፡የእኩይ ሥራቸው መራራ ፍሬዎች ከሆኑት መጻሕፍቶቻቸውም መካከል ‹‹የአዲሰ ኪዳን መካከለኛ» የተባለው መጽሐፍ በመጽሐፍ ቅዱስ ሲመዘን ቀሎ የተገኘ /ከፍሬው ገለባ/ መሆኑንም መጽሐፍ ቅዱስን ምስክር አድርገን አሳይተናል፡፡እንዲሁም