ከቁጥር አራት የቀጠለ
የተወደዳችሁ አንባብያን!
እንደምን ሰነበታችሁ ?
ባለፈው በክፍል አራት ጽሁፋችን የካህናትን አገልግሎት በሚመለከት ጽሁፍ እንመለሳለን ባልነው መሰረት እነሆ ዛሬ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ካቆምንበት “‹‹የአዲሰ ኪዳን መካከለኛ» በመጽሐፍ ቅዱስ ሲመዘን ” ብለን በጀመርነው ርዕስ እንቀጥላለን፡፡
- ከመጽሐፉ ከገጽ 8 የተወሰደ ፦ ‹‹…ዛሬም በሰው ሥርዓት የተሸሙትን ምድራውያን ካህናት አልፈን በመምጣት እግዚአብሔር በሾመው ሰማያዊ ሊቀካህን እግር ሥር እንውደቅ፤ምሕረትም እናገኛለን፡፡››
- ከመጽሐፉ ከገጽ 12 የተወሰደ ፦ ‹‹…በመሆኑም በወንጌል ቃል ለተገለጠው እውነት ታማኝ ሊሆኑ ባልቻሉት በዘመናችን አሮኖችና ኤሊዎች መገልገልን ትተን በሰማያዊት መቅደስ እግዚአብሔር ወዳስቀመጠልን ወደታመነው ሊቀካህናት ወደ ኢየሱስ ዘንድ ልንኮበልል ያሰፈልጋል፡፡››
- ከመጽሐፉ ከገጽ 17 የተወሰደ ፦ ‹‹ከክርስቶስ ወደ ሐዋርያት ከሐዋርያት ወደ ተከታዮቻቸው እየተባለ ሲወርድ ሲዋረድ እስከ ዘመናችን የደረሰ የተለየ የክህነት መስመር የለም፡፡››
በማለት
ለጻፉት ክህደታቸው ምላሽ የሚሆኑትን የሚከተሉትን የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች እንመልከት ፦