Sunday, December 13, 2015

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤15 ክፍል አስራ ሦስት

ከቁጥር አስራ ሁለት የቀጠለ

የተወደዳችሁ አንባብያን!
እንደምን ሰነበታችሁ ?

‹‹ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ›› በሚለው ዐቢይ ርዕስ ሥር፤ በክፍል አስራ አንድና አስራ ሁለት ላይ ወቅታዊ የሆነውን የኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን የውስጥና የውጪ መናፍቃን/ተሐድሶዎች/ ችግር በማስመልከት ማህበረ ቅዱሳን በድረ-ገጹ (www.eotcmk.org) ያቀረበውን ዘገባ ተመልክታችሁ ጥሩ ግንዛቤ እንዳገኛችሁ በመገመት፤በመቀጠል ደግሞ "የተሐድሶ መረብ አድማስና የትኩረት አቅጣጫ" "ንቁ ሳይሆን ተናነቁ" "መንፈሳዊ ኮሌጆችና ደቀ መዛሙርቱ ምንና ምን ናቸው?" በሚሉት ርዕሶች ከማህበረ ቅዱሳን ያገኘነውን በማስረጃ የተደገፈ ዘገባ እነሆ ብለናል፡፡ 

ማስገንዘቢያ፤

የተከበራችሁ አንባብያን የቤተ ክርስቲያን አምላክ ልዑል እግዚአብሔር አስቀድሞ በቅዱስ ወንጌል እንዲሁም በየጊዜው ደግሞ በተለያየ መንገድ የሚናገረን እራሳችንንም ሆነ ሌላውን ከስህተት ጎዳና እንድንጠብቅ ነው፡፡ስለሆነም እያንዳንዳችን የቤ/ክ ልጆች "ከእኔ ምን ይጠበቃል?"ብለን በመጠየቅ የቤ/ክ እምነት፣ሥርዓትና ትውፊት ከአባቶቻችን በተረከብነው መሠረት እንዲቀጥል ለማድረግ በጾምና በጸሎት ከመታገዝ ጋር አቅማችን የሚችለውን ሁሉ በማድረግ መንፈሳዊ ግዴታችንን እንድንወጣ በቅዱሳን አምላክ በልዑል እግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን፡፡

መልካም ንባብ!

Thursday, December 3, 2015

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤15 ክፍል አስራ ሁለት

የተወደዳችሁ አንባብያን!
እንደምን ሰነበታችሁ ?
     ‹‹ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ›› በሚለው ዐቢይ ርዕስ በክፍል አስራ አንድ ላይ ወቅታዊ የሆነውን የኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን  (የውስጥና የውጪ መናፍቃን) ችግር በማስመልከት ማህበረ ቅዱሳን በድረ-ገጹ (www.eotcmk.org) " የተሐድሶን ምንነት ሳታውቁ፣ ስለ ተሐድሶዎች ማንነት አትጠይቁ!! " በሚል ርዕስ ያሰፈረውን በማስረጃ የተደገፈ ዘገባ አንብባችሁ ጥሩ ግንዛቤ እንዳገኛችሁ እናምናለን፡፡

     ከዚህ በመቀጠል ደግሞ እነዚሁ ሃይማኖት እናድሳለን ባዮች በቤተ ክርስቲያናችን ላይ እያደረሱ ያለውን ችግር ማህበረ ቅዱሳን በድረ-ገጹ (www.eotcmk.org) በተከታታይ ያቀረበውን ቀጣይ ጽሁፍ ባለበት ሁኔታ /እንዳለ/ አቅርበነዋል፡፡
ማስገንዘቢያ፤
     የተከበራችሁ አንባብያን የቤተ ክርስቲያን አምላክ አስቀድሞ በወንጌል እንዲሁም በየጊዜው ደግሞ በአንድም በሌላም መንገድ የሚናገረን እራሳችንንም ሆነ ሌላውን ከስህተት ጎዳና እንድንጠብቅ ነው፡፡ስለሆነም እያንዳንዳችን "ከእኔ ምን ይጠበቃል?"ብለን በመጠየቅ የቤ/ክ እምነት፣ሥርዓትና ትውፊት ከአባቶቻችን በተረከብነው መሠረት እንዲቀጥል ለማድረግ በጾምና በጸሎት ከመታገዝ ጋር አቅማችን የሚችለውን ሁሉ በማድረግ መንፈሳዊ ግዴታችንን እንድንወጣ በቅዱሳን አምላክ በልዑል እግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን፡፡
መልካም ንባብ!

Sunday, November 22, 2015

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤15 ክፍል አስራ አንድ

ከቁጥር አስር የቀጠለ
የተወደዳችሁ አንባብያን!
እንደምን ሰነበታችሁ ?

‹‹ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ›› በሚለው ዐቢይ ርዕስ ሥር ከክፍል አንድ እስከ ዘጠኝ ባስነበብነው ጽሁፍ የዘመናችን የቤተ ክርስቲያናችን ትልቅ ፈተና የሆኑትን እራሳቸውን ‹‹ተሐድሶ ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ››ብለው የሚጠሩትን የበግ ለምድ የለበሱ ተኩላዎችን የጥፋት ተልእኮ ለማሳየት ሞክረናል፡፡የእኩይ ሥራቸው ፍሬዎች ከሆኑት መጻሕፍቶቻቸውም መካከል ‹‹የአዲሰ ኪዳን መካከለኛ» የተባለው መጽሐፍ በመጽሐፍ ቅዱስ ሲመዘን ቀሎ የተገኘ /ከፍሬው ገለባ/ መሆኑንም መጽሐፍ ቅዱስን ምስክር አድርገን አሳይተናል፡፡እንዲሁም በክፍል አስር "ቢኒ ዘልደታ" የተባሉት ወንድማችን ያዘጋጁትን ወቅታዊ የተሐድሶ መናፍቃን እንቅስቃሴ የሚገልጽ ጽሁፋቸውን አስነብበናችኋል፡፡
ከዚህ በመቀጠል ደግሞ ስለዚሁ ወቅታዊና ፈታኝ ስለሆነው የኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን ችግር (የውስጥና የውጪ መናፍቃን) ጉዳይ ማህበረ ቅዱሳን በድረ-ገጹ (www.eotcmk.org) " የተሐድሶን ምንነት ሳታውቁ፣ ስለ ተሐድሶዎች ማንነት አትጠይቁ!! " በሚል ርዕስ ያሰፈረውን በማስረጃ የተደገፈ ዘገባ ምንም ሳንጨምርና ሳንቀንስ አቅርበነዋል፡፡
መልካም ንባብ!

Sunday, August 9, 2015

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤15 ክፍል አስር

በስም አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

የተከበራችሁ የዚህ ድረ ገጽ ታዳሚዎች! እንደምን ሰነበታችሁ?
በክፍል ስምንትና በክፍል ዘጠኝ ዘገባችን "ከሐሰተኛው መምህር" ተጠበቁ በሚል ንዑስ ርዕስ ስለ ሰሎሞን ዮሐንስ የምንፍቅና ትምህርት አስነብበናችሁ በይቀጥላል አቆይተነው እንደነበር ይታወሳል፡፡ሆኖም አሁን ባለበት ደብር ምን እየሰራ እንደሆነ ተክክለኛውን ጭብጥ አግኝተን እስከምናቀርብላችሁ ድረስ፤ ለዛሬው ስለ ተሐድሶ መናፍቃን ወቀታዊ የጥፋት እንቅስቃሴ Bini Zelideta የተባሉት የቤ/ክ ልጅ ያዘጋጁትንና በማህበራዊ ድረ ገጽ ያስነበቡንን ጽሁፍ ትምህርት ሰጪ ሆኖ ስላገኘነው ምንም ሳንጨምርና ሳነቀንስ አቅርበነዋል፡፡
ልዑል እግዚአብሔር ቅድስት ተዋሕዶ ሃይማኖታችንን ከከሃድያንና ከመናፍቃን የስህተት ትምህርት ይጠበቅልን!!!



Bini Zelideta

“ተሃድሶ የወቅቱ የቤተ ክርስቲያን ፈተና”
ጠላት ዲያቢሎስ ኦርቶዶክሳዊት ቤ/ክ ላይ ያላዘመተው ሠራዊት ፣ ያልሰነዘረው ፈተና አለ ለማለት አይቻልም ፡፡ በየጊዜው ስልቱን እየቀያየረ የሚቃጣባት ፈተና ከጊዜ ወደ ጊዜ እየከረረ መምጣቱ ዲያቢሎስ ጊዜው እንደተፈጸመበት ዐውቆ ያለ የሌለ ኃይሉን በመጠቀም ላይ መሆኑን ያሳያል፡፡

Sunday, June 28, 2015

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤15 ክፍል ዘጠኝ

በስም አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

ከሐሰተኛው ‹‹መምህር›› ተጠበቁ!

የተከበራችሁ አንባብያን!
በክፍል ስምንት ዘገባችን ስለ አንድ የውስጥ መናፍቅ /ሰሎሞን ዮሐንስ/ የኑፋቄ ሥራ በከፊል ማስነበባችን ይታወሳል፡፡ከዚህ ጦማር አንባብያን በተሰጠን አስተያየት  መሰረት ግለሰቡ ከስራ የታገደባቸውን ቃለ ጉባኤዎች ከዚህ በታች አቅርበናል፡፡

/ በየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን፦
ገጽ 1

ገጽ 2

Sunday, May 10, 2015

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤15 ክፍል ስምንት

በስም አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

ከሐሰተኛው ‹‹መምህር›› ተጠበቁ!

የተከበራችሁ አንባብያን!

“የበግ ለምድ ለብሰው ከሚመጡባችሁ በውስጣቸው ግን ነጣቂዎች ተኩላዎች ከሆኑ ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡ ከፍሬያቸው ታውቋቸዋላችሁ፡፡ ከእሾህ ውይን ክኩርንችትስ በለስ ይለቀማልን ? እንዲሁ መልካም ዛፍ ሁሉ መልካም ፍሬ ያደርጋል፡፡ክፉም ዛፍ ክፉ ፍሬ ያደርጋል፡፡”ማቴ.7፤15-18 የሚለውን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ክፍለ ትምህርት መነሻ ርዕስ አድርገን ባቀረብነው ተከታታይ ጽሁፍ ፤ መናፍቃን /ተሐድሶ ነን ባዮች/ በውስጥም በውጭም ሆነው በኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ሃይማኖታችን ላይ እየዘሩ ያሉትን የኑፋቄ እንክርዳድ በተመለከተ እያንዳንዱ ምዕመን ቢያንስ እራሱን ከስህተት ትምህርታቸው ለመጠበቅ የሚያስችለውን ያህል መጠነኛ ገንዛቤ ለማስጨበጥ ሞክረናል፡፡ወደፊትም እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ እንቀጥላለን፡፡

ለዛሬው ስለ አንድ የውስጥ መናፍቅ የኑፋቄ ሥራ እንመለከታለን፡፡

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤15 ክፍል ሰባት

በመዝሙር ስም ዘፈን! እስከ መቼ ?

የተከበራችሁ የዚህ ድረ ገጽ ታዳሚዎች! እንደምን ሰነበታችሁ?

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” በሚለው ዋና ርዕሳችን ሥር ‹‹በመዝሙር ስም ዘፈን! እስከ መቼ?›› በሚለው ንዑስ ርዕስ የመጀመሪያውን ክፍል መግቢያውን ተመልክተን በይቀጥላል አቆይተነው እንደነበር ይታወሳል፡፡ከዚህ በመቀጠል ደግሞ በ‹‹መዝሙር›› ስም ወደ ቤተ ክርስቲያናችን ሠርጎ ስለገባው ስህተት ትክክለኛ ግንዛቤ እንዲኖረን ከብዙው በጥቂቱ እንመለከታለን፡፡ 
እነዚህ የተለያዩ የጥፋት መልእክተኞችና እኩይ ሥራቸው ቁጥራቸው ከመብዛቱ የተነሳ እያንዳንዳቸውን በዝርዝር ለማየት አስቸጋሪ በመሆኑ ብዙዎቹን ችግሮች አንድ እያልን በሦስት ዋና ዋና ክፍሎች ከፍለን እናያቸዋለን፡፡ምንም እንኳን ከሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን የወጡ እነዚህን ‹‹መዝሙሮች›› ‹‹መዝሙር›› ብለን መጥራት ባይገባንም፤ለጊዜው የምንግባባው በዚሁ ቃል በመሆኑ እኛም ይህንኑ ቃል ተጠቅመን ጽሁፋችንን እንቀጥላለን፡፡