Wednesday, August 21, 2019

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ. ፯፥፲፮ (7፥16) ክፍል አርባ አራት


ከክፍል አርባ ሦስት የቀጠለ፦
የተከበራችሁ የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አባላት!
      ሐዋርያው ቅ/ጳውሎስ በሮሜ መልእክቱ ምዕ.12 ቁጥር 9  “ክፉውን ነገር ተጸየፉት፤ከበጎ ነገር ጋር ተባበሩ” ብሎ ባስተማረን መሠረት፤ዓላማችን አንድ እስከሆነ ድረስ፤ የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ሃይማኖትና ሥርዓት ጠብቀው የሚያስተምሩትን የተለያዩ መምህራንን ትምህርቶች፤በዚች የመወያያ ጦማር ላይ እንድታነቡ ስናደርግ እንደነበረ፤ዛሬም ከ"ልጅ ረድኤት አባተ" ፌስ ቡክ ገጽ ያገኘነውን እጅግ ጠቃሚ ትምህርት እንድታነቡት አቅርበነዋል፡፡በጽሑፉ ላይ አልጨመርንም አልቀነስንም፡፡

Wednesday, August 15, 2018

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ. ፯፥፲፮ (7፥16) ክፍል አርባ ሦስት

ከክፍል አርባ ሁለት የቀጠለ፦
የተከበራችሁ የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አባላት!
      ሐዋርያው ቅ/ጳውሎስ በሮሜ መልእክቱ ምዕ.12 ቁጥር 9  “ክፉውን ነገር ተጸየፉት፤ከበጎ ነገር ጋር ተባበሩ” ብሎ ባስተማረን መሠረት፤ዓላማችን አንድ እስከሆነ ድረስ፤ የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ሃይማኖትና ሥርዓት ጠብቀው የሚያስተምሩትን የተለያዩ መምህራንን ትምህርቶች፤በዚች የመወያያ ጦማር ላይ እንድታነቡ ስናደርግ እንደነበረ እናስታውሳለን፡፡በዚህ ክፍል ደግሞ የዶግማና የቀኖና ጥሰትን በተመለከተ "www.emenetsion.blogspot.com"ከተባለው የጡመራ መድረከ ያገኘነውን በሦስት ክፍል የተዘጋጀ ጠቃሚ የግንዛቤ ማስጨበጫ መልእክት በትዕግስት እንድትመለከቱት እንጋብዛለን፡፡
ጽሁፉን ለንባብ እንዲመች ከማድረግ ውጪ የራሳችንን ሃሳብ አልጨመርንም፡፡
መልካም ንባብ!

Tuesday, August 7, 2018

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ. ፯፥፲፮ (7፥16) ክፍል አርባ ሁለት

ከክፍል አርባ አንድ የቀጠለ፦
የተከበራችሁ የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አባላት!
       እንኳን በጉጉት ለምንጠብቃት ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የፍልሰቷ መታሰቢያ ጾም በሰላምና በጤና አደረሳችሁ አደረሰን፡፡ሁላችንም እንደምናውቀው እመቤታችን በጥር ሃያ አንድ ቀን ባረፈች ጊዜ ቅዱሳን መላእክት የከበረ ሥጋዋን በገነት ውስጥ በምትገኝ በዕፀ ሕይወት ዛፍ ሥር አኑረውት ለሁለት መቶ አምስት ቀናት ቆይቶ፤በነሐሴ አስራ ስድስት ቀን ልጅዋ ወዳጅዋ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋዋንና ነፍሷን አዋሕዶና አስነስቶ በቅዱሳንና በመላእክት ምስጋና ታጅባ ወደ መንግሥተ ሰማያት እንድትገባ አድርጓታል፡፡ከፈጣሪ በታች ከፍጡራን ሁሉ በላይ ክብር ያላት እመቤታችን የአምላክ እናት እንደመሆኗ መጠን ትንሣዔ ዘጉባዔን መጠበቅ ሳያስፈልጋት ከሰው ልጆች ሁሉ ቀድማ መንግሥተ ሰማያት መግባቷ፤ በልጅዋ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ የባሕርይ አምላክነትና በእርሷ አማላጅነት ለምንታመን ለሁላችንም የተጠበቀልን ታላቅ ተስፋ እንዳለን ያረጋግጥልናል፡፡ስለሆነም እኛም የእመቤታችን የአሥራት ልጆች፤በተለይም እትዮጵያውያን፤ ከአባቶቻችን ከሐዋርያት በተቀበልነው ሥርዓት መሠረት በየዓመቱ ከነሐሴ አንድ እስከ ነሐሴ አስራ አምስት ቀን ጾመን በአስራ ስድስተኛው ቀን የእመቤታችን የትንሣዔዋንና የዕርገቷን መታሰቢያ እናከብራለን፡፡
       ይህንን ታሪክ በማስመልከት በዚሁ የጡመራ ገጸችን ክፍል ሃያ ስድስት "በሊቀ ጉባዔ ጌታሁን ደምፀ" የተዘጋጀ፤በአጭር አቀራረብ ብዙ ትምህርት የሚያሰጨብጥ ጽሁፍ አስነብበናችሁ ነበር፡፡አሁን ያለንበት ወቅት ስለ እመቤታችን ብዙ የምነማርበት፣ከሌላው ጊዜ በተለየ ሁኔታ በጾምና በጸሎት ተወስነን በቃል ኪዳኗ የምንማጸንበት ወቅት ላይ ስለሆንን ይህንን የሊቁን ትምህርት አንብበን መንፈሣዊ እውቀታችንንና ሕይወታችንን እንድናጎለምስ ስለሚረዳን በድጋሚ አቅርበነዋል፡፡

Tuesday, May 22, 2018

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤16 ክፍል አርባ አንድ

ከክፍል አርባ የቀጠለ፦

ለዚች ዕለትና ለዚች ሰዓት ያደረሰን የቅዱሳን አምላክ ልዑል እግዚአብሔር ስሙ ይመስገን፡፡

       የተከበራችሁ የኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤ/ክ ልጆች!የመጨረሻው ዘመን የወለዳቸው የተለያዩ መናፍቃን ከውስጥም ከውጭም ሆነው  የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ሃይማኖታችንን እምነት፣ ሥርዓትና እንዲሁም ትውፊት ሳይቀር የሚያፋለሱ የስህተት ትምህርቶች በቤተ ክርስቲያናችን ስም እያሰራጩና ብዙዎችንም እያሳሳቱ መሆኑን ወቅታዊውን የቤ/ክ ሁኔታ በቅርበት የሚከታተል ሁሉ ችግሩን በቀላሉ ሊረዳው ይችላል፡፡እኛም ይህችን "ወልድ ዋሕድ" የተሰኘች የጡመራ መድረክ የጀመርንበት ዋናው ምክንያት፤እነዚህን የጨለማ ሥራዎቻቸውን /የምንፍቅና ትምህርታቸውን/ ወደ ብርሃን በማምጣት ማለትም ስህተታቸውን በመግለጥና አቅማችንና እውቀታችን በሚፈቅድልን መጠን  መልስ በመስጠት፤ ትውልዱ እራሱንም ሆነ ቤተ ክርስቲያኑን ከስህተቱ ትምህርት እንዲጠብቅ የሚያስችለውን ግንዛቤ ለማስጨበጥ ነው፡፡
       እነዚህ የስህተት ትምህርቶች በአብዛኛው የሚያጠነጥኑት በምሥጢረ ሥጋዌ (ከሦስቱ ቅዱስ አንዱ ቅዱስ እግዚአብሔር ወልድ የሰውን ሥጋ ተዋሕዶ ሰውን ያዳነበት ምሥጢር) ትምህርት ላይ ነው፡፡ይህንንም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ሥጋዌው ባስተማረው ትምህርት (ማቴ.24 በሙሉ ይመልከቱ)፤በመጨረሻው ዘመን ብዙ ሐሰተኞች አስተማሪዎች በስሙ እንደሚመጡና ብዙዎችንም እንደሚያስቱ፤እኛም በክርስቶስ ክርስቲያን የተባልን ሁሉ ከስህተት ትምህርታቸው እንድንጠበቅ አስጠንቅቆናል፡፡በመቀጠልም ይህንን የጌታችንን ትምህርት መሠረት በማድረግ "ወደ ዓለም ሂዱ ወንጌልን ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ" ብሎ እሱ በመረጣቸው በሐዋርያትና በእነሱ እግር በተተኩ መምህራንም በየዘመኑ ለተነሳው ትውልድ ትምህርቱና ማስጠንቀቂያው ሲነገር የነበረ ወደፊትም እስከ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሲነገር የሚኖር ነው፡፡ይሁን እንጂ ስንቶቻችን ይህንን ችግር ተረድተናል? ምን ያህልስ እራሳችንንም ሆነ ሌላውን ከስህተት ለመጠበቅ ተዘጋጅተናል? የሚለውን ጥያቄ እራሳችንን እየጠየቅን ከእኛ የሚጠበቀውን ሁሉ ለመፈጸም ዝግጁዎች መሆን ይገባናል፡፡
       ወደ ዋናው ነገር እንመለስና፤ እነዚህን የስህተት ትምህርቶች ከሚያስተላልፉት የእምነት ድርጅቶች አንዱ እራሱን "የእውነት ቃል አገልግሎት"ብሎ የሚጠራው የመናፍቃን ድርጅት ሲሆን፤ከመጽሐፍቻቸው አንዱ በሆነው ‹‹የአዲስ ኪዳን መካከለኛ» በተባለው መጽሐፋቸው በምሥጢረ ሥጋዌ ላይ የሚሰጡትን የክህደት ትምህርት በዚችው ጡመራ መድረክ ከክፍል ሦስት እስከ ክፍል አምስት ከብዙው በጥቂቱ ለማሳየት ሞክረናል፡፡ ይህ ድርጅት ቀድሞ ከእኛ ዘንድ በነበሩ ነገር ግን ከእኛ ወገን ስላልነበሩ በራሳቸው ፈቃድ በወጡ የፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ እምነት አራማጆች የተመሠረተ ሲሆን ድርጅቱ በ2004 ዓ.ም በቅዱስ ሲኖዶስ የተወገዘ ነው፡፡

የተወደዳችሁ አንባብያን፤

       “ክፉውን ነገር ተጸየፉት፤ከበጎ ነገር ጋር ተባበሩ” በማለት ሐዋርያው ቅ/ጳውሎስ በሮሜ መልእክቱ ምዕ.12 ቁጥር 9  በሰፊው አስተምሮናል፡፡በዚሁ መሠረት ዝግጅቱ የእኛ ባይሆንም፤ትክክለኛውን የተዋሕዶ ትምህርት የሚያስተምሩትን የሌሎች መምህራን ትምህርቶች ስናካፍላችሁ እንደነበር፤ዛሬም "ኢየሱስ ክርስቶስ ያማልዳል" (ሎቱ ስብሐት) እያሉ ለሚዘባርቁ የተለያዩ የውስጥም ሆነ የውጭ መናፍቃን ተገቢውን ምላሽ የሰጡበትንና "ፀረ-በጋሻው ደሳለኝ ፀረ-ተሀድሶ!" በተባለው የፌስ ቡክ ገጽ ለንባብ የበቃውን የመልአከ ሰላም ቀሲስ ደጀኔ ሺፈራውን ትምህርት እንዳለ አቅርበንላችሁዋል፡፡

መልካም ንባብ ከማስተዋል ጋር!

Thursday, April 5, 2018

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤16 ክፍል አርባ

ከክፍል ሰላሳ ዘጠኝ የቀጠለ፦
ዐቢይ ጾምን በሰላምና በጤና አስፈጽሞ ለዚች ቀንና ሰዓት ያደረሰን ልዑል እግዚአብሔር ስሙ የተመሰገነ ይሁን፡፡
የተከበራችሁ የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ልጆች!
ከዚህ በመቀጠል፤ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ እኛ ስለ ሰው ልጆች ሲል ለሞት ተላልፎ የተሰጠባትን   ምሴተ ሐሙስን  በማስመልከት በወንድማችን በ"አክሊሉ ደበላ" የተዘጋጀች ድንቅ ግጥም አቅርበንላችኋል፡፡

Saturday, February 24, 2018

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤16 ክፍል ሰላሳ ዘጠኝ

ከክፍል ሰላሳ ስምንት የቀጠለ፦

የተከበራችሁ የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ልጆች!

እንኳን ለእናታችን ለወላዲተ አምላክ ለቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ የቃል ኪዳን በዓል አደረሳችሁ አደረሰን፡፡

     ከዚህ በመቀጠል ስለ እመቤታችን ክብር ተናግረው የማይጠግቡት፤በተለይም ውዳሴዋንና ቅዳሴዋን በመተርጎምና የዘመኑን ቴክኖሎጂ በመጠቀም ሁላችንም በየቤታችን እንድንሰማውና እንድንማርበት እንድንቀደስበትም በሲዲ አዘጋጅተው ያበረከቱልን መምህራችን ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን ደምፀ፤ የእመቤታችንን የኪዳነ ምሕረት በዓል በማስመልከት በማሕበራዊ ድረ-ገጽ ያስተላለፉትን ትምህርት ከዚህ ቀጥሎ አቅርበንላችኋል፡፡

Sunday, February 11, 2018

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤16 ክፍል ሰላሳ ስምንት

ከክፍል ሰላሳ ሰባት የቀጠለ፦
     የተወደዳችሁ አንባብያን! እንኳን የካቲት አምስት ቀን 2010 ዓ.ም ለምንጀምረው ዐቢይ ጾም  በሰላምና በጤና አደረሳችሁ አደረሰን፡፡
     ከዚህ በመቀጠል ስለ ዐቢይ ጾም መጠነኛ ግንዛቤ የምናገኝበት ትምህርት፤እንዲሁም በዐቢይ ጾም ውስጥ በሚውሉት ስምንት ሰንበታት  /እሑዶች/ በቅዳሴ ጊዜ የሚነበቡትን ምንባባት በተመለከተ በዝርዝር አቅርበንላችኋልና በጥሞና እንድትከታተሉት እንጋብዛለን፡፡