Sunday, March 27, 2016

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤15 ክፍል አስራ አምስት

ከክፍል አስራ አራት የቀጠለ
"እያወቁ ማለቅ"
"ያላወቁ አለቁ ነበረ ተረቱ፤
እያወቁ ማለቅ መጣ በሰዓቱ፡፡"
     በሰማይም ሆነ በምድር ላይ ሁሉን ቻይ ከሆነው ከልዑል እግዚአብሔር እውቅና እና ፈቃድ ውጪ የሚከናወን ምንም ነገር እንደሌለ ይታወቃል፡፡ይታመናልም፡፡ይሁን እንጂ  ለስሙ ክብር ምስጋና ይግባውና አምላካችን እግዚአብሔር ሰውን ከሌሎች ፍጡራን ለይቶ በመልኩና በምሳሌው ሲፈጠረው የማሰብ፣የመናገርና ሕያው ሆኖ የመኖር ዕድል ሰጥቶታል፡፡የሰው ልጅ በዚህ በተሰጠው አእምሮ መመራት አቅቶት በኃጢአት ቢወድቅ፤ይህንን አድርግ ይህንን አታድርግ የሚል የተጻፈ ህግ /ህገ ኦሪትን/ ሰጠው፡፡በዚህ ብቻ አላበቃም፤እራሱ እግዚአብሔር ወልድ ወደዚች ምድር መጥቶ ለሰው ልጅ የቤዛነቱንና የአርአያነት ሥራውን ፈጸሞለታል፡፡ ጌታችን መድሐኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በጽንስ ጀምሮ በመሰቀል የፈጸመውን የቤዛነቱን ሥራ እፁብ! ድንቅ! ብሎ ከማመስገን በስተቀር በዚች አጭር ጽሁፍ የምንለው ነገር አይኖረንም፡፡በአርአያነት/በምሳሌነት/ ሥራው ግን ከኃጢአት በስተቀር የሰውን ህግ ሁሉ ፈጽሞ እኛም እንድንከተለው አዝዞናል፡፡በእኔ ያመነ እኔ የምሰራውን ሁሉ ያደርጋል፤እንደውም የበለጠ ያደርጋል ብሎ፡፡ዮሐ.14፥12፡፡

Sunday, March 6, 2016

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤15 ክፍል አስራ አራት

የተወደዳችሁ አንባብያን!
እንደምን ሰነበታችሁ ?
‹‹ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ›› በሚለው ዐቢይ ርዕስ ሥር፤ በክፍል አስራ አንድና አስራ ሁለት ላይ ወቅታዊ የሆነውን የኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን  የውስጥና የውጪ መናፍቃን/ተሐድሶዎች/ ችግር በማስመልከት ማህበረ ቅዱሳን በድረ-ገጹ (www.eotcmk.org) ያቀረበውን ዘገባ ተመልክታችሁ ጥሩ ግንዛቤ እንዳገኛችሁ በመገመት፤በመቀጠል ደግሞ "አምልኮተ ሰይጣን - ፍጻሜ “ተሐድሶ”?"
በሚለው ርዕስ ከማህበረ ቅዱሳን ድረ-ገጽ ያገኘነውን በማስረጃ የተደገፈ ዘገባ እነሆ ብለናል፡፡

መልካም ንባብ!

Sunday, December 13, 2015

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤15 ክፍል አስራ ሦስት

ከቁጥር አስራ ሁለት የቀጠለ

የተወደዳችሁ አንባብያን!
እንደምን ሰነበታችሁ ?

‹‹ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ›› በሚለው ዐቢይ ርዕስ ሥር፤ በክፍል አስራ አንድና አስራ ሁለት ላይ ወቅታዊ የሆነውን የኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን የውስጥና የውጪ መናፍቃን/ተሐድሶዎች/ ችግር በማስመልከት ማህበረ ቅዱሳን በድረ-ገጹ (www.eotcmk.org) ያቀረበውን ዘገባ ተመልክታችሁ ጥሩ ግንዛቤ እንዳገኛችሁ በመገመት፤በመቀጠል ደግሞ "የተሐድሶ መረብ አድማስና የትኩረት አቅጣጫ" "ንቁ ሳይሆን ተናነቁ" "መንፈሳዊ ኮሌጆችና ደቀ መዛሙርቱ ምንና ምን ናቸው?" በሚሉት ርዕሶች ከማህበረ ቅዱሳን ያገኘነውን በማስረጃ የተደገፈ ዘገባ እነሆ ብለናል፡፡ 

ማስገንዘቢያ፤

የተከበራችሁ አንባብያን የቤተ ክርስቲያን አምላክ ልዑል እግዚአብሔር አስቀድሞ በቅዱስ ወንጌል እንዲሁም በየጊዜው ደግሞ በተለያየ መንገድ የሚናገረን እራሳችንንም ሆነ ሌላውን ከስህተት ጎዳና እንድንጠብቅ ነው፡፡ስለሆነም እያንዳንዳችን የቤ/ክ ልጆች "ከእኔ ምን ይጠበቃል?"ብለን በመጠየቅ የቤ/ክ እምነት፣ሥርዓትና ትውፊት ከአባቶቻችን በተረከብነው መሠረት እንዲቀጥል ለማድረግ በጾምና በጸሎት ከመታገዝ ጋር አቅማችን የሚችለውን ሁሉ በማድረግ መንፈሳዊ ግዴታችንን እንድንወጣ በቅዱሳን አምላክ በልዑል እግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን፡፡

መልካም ንባብ!

Thursday, December 3, 2015

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤15 ክፍል አስራ ሁለት

የተወደዳችሁ አንባብያን!
እንደምን ሰነበታችሁ ?
     ‹‹ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ›› በሚለው ዐቢይ ርዕስ በክፍል አስራ አንድ ላይ ወቅታዊ የሆነውን የኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን  (የውስጥና የውጪ መናፍቃን) ችግር በማስመልከት ማህበረ ቅዱሳን በድረ-ገጹ (www.eotcmk.org) " የተሐድሶን ምንነት ሳታውቁ፣ ስለ ተሐድሶዎች ማንነት አትጠይቁ!! " በሚል ርዕስ ያሰፈረውን በማስረጃ የተደገፈ ዘገባ አንብባችሁ ጥሩ ግንዛቤ እንዳገኛችሁ እናምናለን፡፡

     ከዚህ በመቀጠል ደግሞ እነዚሁ ሃይማኖት እናድሳለን ባዮች በቤተ ክርስቲያናችን ላይ እያደረሱ ያለውን ችግር ማህበረ ቅዱሳን በድረ-ገጹ (www.eotcmk.org) በተከታታይ ያቀረበውን ቀጣይ ጽሁፍ ባለበት ሁኔታ /እንዳለ/ አቅርበነዋል፡፡
ማስገንዘቢያ፤
     የተከበራችሁ አንባብያን የቤተ ክርስቲያን አምላክ አስቀድሞ በወንጌል እንዲሁም በየጊዜው ደግሞ በአንድም በሌላም መንገድ የሚናገረን እራሳችንንም ሆነ ሌላውን ከስህተት ጎዳና እንድንጠብቅ ነው፡፡ስለሆነም እያንዳንዳችን "ከእኔ ምን ይጠበቃል?"ብለን በመጠየቅ የቤ/ክ እምነት፣ሥርዓትና ትውፊት ከአባቶቻችን በተረከብነው መሠረት እንዲቀጥል ለማድረግ በጾምና በጸሎት ከመታገዝ ጋር አቅማችን የሚችለውን ሁሉ በማድረግ መንፈሳዊ ግዴታችንን እንድንወጣ በቅዱሳን አምላክ በልዑል እግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን፡፡
መልካም ንባብ!

Sunday, November 22, 2015

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤15 ክፍል አስራ አንድ

ከቁጥር አስር የቀጠለ
የተወደዳችሁ አንባብያን!
እንደምን ሰነበታችሁ ?

‹‹ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ›› በሚለው ዐቢይ ርዕስ ሥር ከክፍል አንድ እስከ ዘጠኝ ባስነበብነው ጽሁፍ የዘመናችን የቤተ ክርስቲያናችን ትልቅ ፈተና የሆኑትን እራሳቸውን ‹‹ተሐድሶ ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ››ብለው የሚጠሩትን የበግ ለምድ የለበሱ ተኩላዎችን የጥፋት ተልእኮ ለማሳየት ሞክረናል፡፡የእኩይ ሥራቸው ፍሬዎች ከሆኑት መጻሕፍቶቻቸውም መካከል ‹‹የአዲሰ ኪዳን መካከለኛ» የተባለው መጽሐፍ በመጽሐፍ ቅዱስ ሲመዘን ቀሎ የተገኘ /ከፍሬው ገለባ/ መሆኑንም መጽሐፍ ቅዱስን ምስክር አድርገን አሳይተናል፡፡እንዲሁም በክፍል አስር "ቢኒ ዘልደታ" የተባሉት ወንድማችን ያዘጋጁትን ወቅታዊ የተሐድሶ መናፍቃን እንቅስቃሴ የሚገልጽ ጽሁፋቸውን አስነብበናችኋል፡፡
ከዚህ በመቀጠል ደግሞ ስለዚሁ ወቅታዊና ፈታኝ ስለሆነው የኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን ችግር (የውስጥና የውጪ መናፍቃን) ጉዳይ ማህበረ ቅዱሳን በድረ-ገጹ (www.eotcmk.org) " የተሐድሶን ምንነት ሳታውቁ፣ ስለ ተሐድሶዎች ማንነት አትጠይቁ!! " በሚል ርዕስ ያሰፈረውን በማስረጃ የተደገፈ ዘገባ ምንም ሳንጨምርና ሳንቀንስ አቅርበነዋል፡፡
መልካም ንባብ!

Sunday, August 9, 2015

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤15 ክፍል አስር

በስም አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

የተከበራችሁ የዚህ ድረ ገጽ ታዳሚዎች! እንደምን ሰነበታችሁ?
በክፍል ስምንትና በክፍል ዘጠኝ ዘገባችን "ከሐሰተኛው መምህር" ተጠበቁ በሚል ንዑስ ርዕስ ስለ ሰሎሞን ዮሐንስ የምንፍቅና ትምህርት አስነብበናችሁ በይቀጥላል አቆይተነው እንደነበር ይታወሳል፡፡ሆኖም አሁን ባለበት ደብር ምን እየሰራ እንደሆነ ተክክለኛውን ጭብጥ አግኝተን እስከምናቀርብላችሁ ድረስ፤ ለዛሬው ስለ ተሐድሶ መናፍቃን ወቀታዊ የጥፋት እንቅስቃሴ Bini Zelideta የተባሉት የቤ/ክ ልጅ ያዘጋጁትንና በማህበራዊ ድረ ገጽ ያስነበቡንን ጽሁፍ ትምህርት ሰጪ ሆኖ ስላገኘነው ምንም ሳንጨምርና ሳነቀንስ አቅርበነዋል፡፡
ልዑል እግዚአብሔር ቅድስት ተዋሕዶ ሃይማኖታችንን ከከሃድያንና ከመናፍቃን የስህተት ትምህርት ይጠበቅልን!!!



Bini Zelideta

“ተሃድሶ የወቅቱ የቤተ ክርስቲያን ፈተና”
ጠላት ዲያቢሎስ ኦርቶዶክሳዊት ቤ/ክ ላይ ያላዘመተው ሠራዊት ፣ ያልሰነዘረው ፈተና አለ ለማለት አይቻልም ፡፡ በየጊዜው ስልቱን እየቀያየረ የሚቃጣባት ፈተና ከጊዜ ወደ ጊዜ እየከረረ መምጣቱ ዲያቢሎስ ጊዜው እንደተፈጸመበት ዐውቆ ያለ የሌለ ኃይሉን በመጠቀም ላይ መሆኑን ያሳያል፡፡

Sunday, June 28, 2015

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤15 ክፍል ዘጠኝ

በስም አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

ከሐሰተኛው ‹‹መምህር›› ተጠበቁ!

የተከበራችሁ አንባብያን!
በክፍል ስምንት ዘገባችን ስለ አንድ የውስጥ መናፍቅ /ሰሎሞን ዮሐንስ/ የኑፋቄ ሥራ በከፊል ማስነበባችን ይታወሳል፡፡ከዚህ ጦማር አንባብያን በተሰጠን አስተያየት  መሰረት ግለሰቡ ከስራ የታገደባቸውን ቃለ ጉባኤዎች ከዚህ በታች አቅርበናል፡፡

/ በየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን፦
ገጽ 1

ገጽ 2