Friday, April 29, 2016

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤15 ክፍል አስራ ሰባት

ከክፍል አስራ ስድስት የቀጠለ

የተከበራቸሁ አንባብያን!
በዚህ የመወያያ መድረክ (ወልድ ዋሕድ) ክፍል ስድስትና ሰባት ቤተ ክርስቲያናችን በመዝሙር በኩል እየገጠማት ያለውን ፈተና በማስመልከት ባቀረብነው ጽሁፍ መጠነኛ ግንዛቤ እንዳገኛችሁ እናምናለን፡፡እንዲሁም በክፍል አስራ ስድስት ደግሞ "Bini Zelideta" ከተባሉ ወንድማችን ከፌስ ቡክ ገጻቸው ላይ ያገኘነውን ጽሁፍ ጥሩ አስተማሪ ሆኖ ስላገኘነው ምንም ሳንጨምርና ሳንቀንስ አስነብበናችኋል፡፡አሁንም ከዚህ በመቀጠል  ደግሞ የ"Blni Zelideta"ን ክፍል ሁለት መዝሙር ነክ ጽሁፍ አቅርበንላቸኋል!!!
መልካም ንባብ!

Sunday, March 27, 2016

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤15 ክፍል አስራ ስድስት

ከክፍል አስራ አምስት የቀጠለ
የተከበራቸሁ አንባብያን!
በዚህ የመወያያ መድረክ (ወልድ ዋሕድ) ክፍል ስድስትና ሰባት ቤተ ክርስቲያናችን በመዝሙር በኩል እየገጠማት ያለውን ፈተና በማስመልከት ባቀረብነው ጽሁፍ መጠነኛ ግንዛቤ እንዳገኛችሁ እናምናለን፡፡ከዚህ በመቀጠል ደግሞ "Bini Zelideta" ከተባሉ ወንድማችን ከፌስ ቡክ ገጻቸው ላይ ያገኘነውን ጽሁፍ አስተማሪ ሆኖ ስላገኘነው እንድታነቡት እንጋብዛለን፡፡
መልካም ንባብ!
Bini Zelideta
የተሃድሶ መናፍቃን መዝሙራት ሥውር ተልዕኮ!”
ክፍል-1 (ስለ ነገረ ክርስቶስ) /መልዕክቱ የረዘመው ግጥሞች ስለበዙበት ነው/
መግቢያ
ቅድስት፤ኦርቶዶክሳዊት ሃይማኖታችን ዕረፍት አልባ ዘመናትን ስታሳልፍ ዛሬ 2008 ዓመቷ ነው፡፡ ፈተናዎቿም እንደየ አዝማናቱና እንደፈታኞቿ የተለያዩ ነበሩ፡፡ ሠይፍ፣የዐላውያን መከራ፣የአናብሥት ትግል፣የክርስቲያኖች ስቃይ የሮም ኮሎሲየም አምፊ ቴአትር ትርዒት፣የቁም እሳት ቃጠሎ፣የካታኮምቡ ሕይወት፣የሠንሠለት ኑሮ እና የመንኩራኩር ስቃይ የመጀመሪያው እልህ አስጨራሽ ፈተናዋ ሲሆን እግር ተከትሎ፤ዓይነቱን ቀይሮ የመጣው የአርዮሳውያን ሃይማኖትን የመቀየር፣አስተምሕሮዋን የመበረዝ እንቅስቃሴ ጣሯን፣ሰቀቀኗን፣መከራዋን አብዝቶባት ቆይቷል፡፡ ዮዲት ጉዲት፣የካቶሊክ ሚሲዮናውያን፣ጽንፈኛ አሕዛቦችና የሉተር ርዝራዦች ዞረው ዞረው ሲሻቸው አንድ ላይ ሲሻቸው ደግሞ በፍርርቅ በመከረኛይቱ ሃይማኖት ላይ ቀንበር ሲጭኑ ኖረዋል ዛሬም ዕረፍት የላትም! የገሃነም ደጆች አይችሉአትም ተብሎ ስለተጻፈው አማናዊ ቃል ሁሉን አልፋ ዛሬ ብትደርስ ለሆዳቸው ያደሩ ሥጋውያን አስተምህሮዋን እናድሳለን ብለው ተነሡባት፡፡ ይህ ከቀደምት ዘመናት በዓይነትም በቅርጽም አካሄዱን ቀይሮ ቤተ ክርስቲያንን የማዳከም ሥልት ይዞ የተነሣው ፕሮቴስታንታዊ ቡድን ስውር ተልዕኮውን በቅድስት ቤተክርስቲያን ላይ በመሰንዘር ከፍተኛ ጥፋት አድርሷል አሁንም በማድረስ ላይ ይገኛል፡፡ የሃይማኖት ቅብ ይዘው፣ተቆርቋሪ መስለው መንገዷን ስታለች፣አስተምህሮዋ ልክ አይደለም፣አርጅታለች፣እናድሳታለን ባዮች ሲሆኑ በትምርቶቻቸው እና ከዘፈን በተቃኙ መዝሙሮቻቸው ትውልድን መበረዝ የዕለት እንጀራቸው አድርገውታል፡፡ በተለይም መዝሙሮቻቸው በአንድ ሌሊት ተደርሰው ንጋቱን ለጆሮ ስለሚበቁ ኑፋቄን ለማሰራጨት ደገኛ መሣሪያቸው ሆኖ በማገልገል ላይ ይገኛል፡፡

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤15 ክፍል አስራ አምስት

ከክፍል አስራ አራት የቀጠለ
"እያወቁ ማለቅ"
"ያላወቁ አለቁ ነበረ ተረቱ፤
እያወቁ ማለቅ መጣ በሰዓቱ፡፡"
     በሰማይም ሆነ በምድር ላይ ሁሉን ቻይ ከሆነው ከልዑል እግዚአብሔር እውቅና እና ፈቃድ ውጪ የሚከናወን ምንም ነገር እንደሌለ ይታወቃል፡፡ይታመናልም፡፡ይሁን እንጂ  ለስሙ ክብር ምስጋና ይግባውና አምላካችን እግዚአብሔር ሰውን ከሌሎች ፍጡራን ለይቶ በመልኩና በምሳሌው ሲፈጠረው የማሰብ፣የመናገርና ሕያው ሆኖ የመኖር ዕድል ሰጥቶታል፡፡የሰው ልጅ በዚህ በተሰጠው አእምሮ መመራት አቅቶት በኃጢአት ቢወድቅ፤ይህንን አድርግ ይህንን አታድርግ የሚል የተጻፈ ህግ /ህገ ኦሪትን/ ሰጠው፡፡በዚህ ብቻ አላበቃም፤እራሱ እግዚአብሔር ወልድ ወደዚች ምድር መጥቶ ለሰው ልጅ የቤዛነቱንና የአርአያነት ሥራውን ፈጸሞለታል፡፡ ጌታችን መድሐኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በጽንስ ጀምሮ በመሰቀል የፈጸመውን የቤዛነቱን ሥራ እፁብ! ድንቅ! ብሎ ከማመስገን በስተቀር በዚች አጭር ጽሁፍ የምንለው ነገር አይኖረንም፡፡በአርአያነት/በምሳሌነት/ ሥራው ግን ከኃጢአት በስተቀር የሰውን ህግ ሁሉ ፈጽሞ እኛም እንድንከተለው አዝዞናል፡፡በእኔ ያመነ እኔ የምሰራውን ሁሉ ያደርጋል፤እንደውም የበለጠ ያደርጋል ብሎ፡፡ዮሐ.14፥12፡፡

Sunday, March 6, 2016

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤15 ክፍል አስራ አራት

የተወደዳችሁ አንባብያን!
እንደምን ሰነበታችሁ ?
‹‹ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ›› በሚለው ዐቢይ ርዕስ ሥር፤ በክፍል አስራ አንድና አስራ ሁለት ላይ ወቅታዊ የሆነውን የኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን  የውስጥና የውጪ መናፍቃን/ተሐድሶዎች/ ችግር በማስመልከት ማህበረ ቅዱሳን በድረ-ገጹ (www.eotcmk.org) ያቀረበውን ዘገባ ተመልክታችሁ ጥሩ ግንዛቤ እንዳገኛችሁ በመገመት፤በመቀጠል ደግሞ "አምልኮተ ሰይጣን - ፍጻሜ “ተሐድሶ”?"
በሚለው ርዕስ ከማህበረ ቅዱሳን ድረ-ገጽ ያገኘነውን በማስረጃ የተደገፈ ዘገባ እነሆ ብለናል፡፡

መልካም ንባብ!

Sunday, December 13, 2015

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤15 ክፍል አስራ ሦስት

ከቁጥር አስራ ሁለት የቀጠለ

የተወደዳችሁ አንባብያን!
እንደምን ሰነበታችሁ ?

‹‹ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ›› በሚለው ዐቢይ ርዕስ ሥር፤ በክፍል አስራ አንድና አስራ ሁለት ላይ ወቅታዊ የሆነውን የኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን የውስጥና የውጪ መናፍቃን/ተሐድሶዎች/ ችግር በማስመልከት ማህበረ ቅዱሳን በድረ-ገጹ (www.eotcmk.org) ያቀረበውን ዘገባ ተመልክታችሁ ጥሩ ግንዛቤ እንዳገኛችሁ በመገመት፤በመቀጠል ደግሞ "የተሐድሶ መረብ አድማስና የትኩረት አቅጣጫ" "ንቁ ሳይሆን ተናነቁ" "መንፈሳዊ ኮሌጆችና ደቀ መዛሙርቱ ምንና ምን ናቸው?" በሚሉት ርዕሶች ከማህበረ ቅዱሳን ያገኘነውን በማስረጃ የተደገፈ ዘገባ እነሆ ብለናል፡፡ 

ማስገንዘቢያ፤

የተከበራችሁ አንባብያን የቤተ ክርስቲያን አምላክ ልዑል እግዚአብሔር አስቀድሞ በቅዱስ ወንጌል እንዲሁም በየጊዜው ደግሞ በተለያየ መንገድ የሚናገረን እራሳችንንም ሆነ ሌላውን ከስህተት ጎዳና እንድንጠብቅ ነው፡፡ስለሆነም እያንዳንዳችን የቤ/ክ ልጆች "ከእኔ ምን ይጠበቃል?"ብለን በመጠየቅ የቤ/ክ እምነት፣ሥርዓትና ትውፊት ከአባቶቻችን በተረከብነው መሠረት እንዲቀጥል ለማድረግ በጾምና በጸሎት ከመታገዝ ጋር አቅማችን የሚችለውን ሁሉ በማድረግ መንፈሳዊ ግዴታችንን እንድንወጣ በቅዱሳን አምላክ በልዑል እግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን፡፡

መልካም ንባብ!

Thursday, December 3, 2015

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤15 ክፍል አስራ ሁለት

የተወደዳችሁ አንባብያን!
እንደምን ሰነበታችሁ ?
     ‹‹ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ›› በሚለው ዐቢይ ርዕስ በክፍል አስራ አንድ ላይ ወቅታዊ የሆነውን የኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን  (የውስጥና የውጪ መናፍቃን) ችግር በማስመልከት ማህበረ ቅዱሳን በድረ-ገጹ (www.eotcmk.org) " የተሐድሶን ምንነት ሳታውቁ፣ ስለ ተሐድሶዎች ማንነት አትጠይቁ!! " በሚል ርዕስ ያሰፈረውን በማስረጃ የተደገፈ ዘገባ አንብባችሁ ጥሩ ግንዛቤ እንዳገኛችሁ እናምናለን፡፡

     ከዚህ በመቀጠል ደግሞ እነዚሁ ሃይማኖት እናድሳለን ባዮች በቤተ ክርስቲያናችን ላይ እያደረሱ ያለውን ችግር ማህበረ ቅዱሳን በድረ-ገጹ (www.eotcmk.org) በተከታታይ ያቀረበውን ቀጣይ ጽሁፍ ባለበት ሁኔታ /እንዳለ/ አቅርበነዋል፡፡
ማስገንዘቢያ፤
     የተከበራችሁ አንባብያን የቤተ ክርስቲያን አምላክ አስቀድሞ በወንጌል እንዲሁም በየጊዜው ደግሞ በአንድም በሌላም መንገድ የሚናገረን እራሳችንንም ሆነ ሌላውን ከስህተት ጎዳና እንድንጠብቅ ነው፡፡ስለሆነም እያንዳንዳችን "ከእኔ ምን ይጠበቃል?"ብለን በመጠየቅ የቤ/ክ እምነት፣ሥርዓትና ትውፊት ከአባቶቻችን በተረከብነው መሠረት እንዲቀጥል ለማድረግ በጾምና በጸሎት ከመታገዝ ጋር አቅማችን የሚችለውን ሁሉ በማድረግ መንፈሳዊ ግዴታችንን እንድንወጣ በቅዱሳን አምላክ በልዑል እግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን፡፡
መልካም ንባብ!

Sunday, November 22, 2015

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤15 ክፍል አስራ አንድ

ከቁጥር አስር የቀጠለ
የተወደዳችሁ አንባብያን!
እንደምን ሰነበታችሁ ?

‹‹ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ›› በሚለው ዐቢይ ርዕስ ሥር ከክፍል አንድ እስከ ዘጠኝ ባስነበብነው ጽሁፍ የዘመናችን የቤተ ክርስቲያናችን ትልቅ ፈተና የሆኑትን እራሳቸውን ‹‹ተሐድሶ ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ››ብለው የሚጠሩትን የበግ ለምድ የለበሱ ተኩላዎችን የጥፋት ተልእኮ ለማሳየት ሞክረናል፡፡የእኩይ ሥራቸው ፍሬዎች ከሆኑት መጻሕፍቶቻቸውም መካከል ‹‹የአዲሰ ኪዳን መካከለኛ» የተባለው መጽሐፍ በመጽሐፍ ቅዱስ ሲመዘን ቀሎ የተገኘ /ከፍሬው ገለባ/ መሆኑንም መጽሐፍ ቅዱስን ምስክር አድርገን አሳይተናል፡፡እንዲሁም በክፍል አስር "ቢኒ ዘልደታ" የተባሉት ወንድማችን ያዘጋጁትን ወቅታዊ የተሐድሶ መናፍቃን እንቅስቃሴ የሚገልጽ ጽሁፋቸውን አስነብበናችኋል፡፡
ከዚህ በመቀጠል ደግሞ ስለዚሁ ወቅታዊና ፈታኝ ስለሆነው የኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን ችግር (የውስጥና የውጪ መናፍቃን) ጉዳይ ማህበረ ቅዱሳን በድረ-ገጹ (www.eotcmk.org) " የተሐድሶን ምንነት ሳታውቁ፣ ስለ ተሐድሶዎች ማንነት አትጠይቁ!! " በሚል ርዕስ ያሰፈረውን በማስረጃ የተደገፈ ዘገባ ምንም ሳንጨምርና ሳንቀንስ አቅርበነዋል፡፡
መልካም ንባብ!