Saturday, February 24, 2018

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤16 ክፍል ሰላሳ ዘጠኝ

ከክፍል ሰላሳ ስምንት የቀጠለ፦

የተከበራችሁ የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ልጆች!

እንኳን ለእናታችን ለወላዲተ አምላክ ለቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ የቃል ኪዳን በዓል አደረሳችሁ አደረሰን፡፡

     ከዚህ በመቀጠል ስለ እመቤታችን ክብር ተናግረው የማይጠግቡት፤በተለይም ውዳሴዋንና ቅዳሴዋን በመተርጎምና የዘመኑን ቴክኖሎጂ በመጠቀም ሁላችንም በየቤታችን እንድንሰማውና እንድንማርበት እንድንቀደስበትም በሲዲ አዘጋጅተው ያበረከቱልን መምህራችን ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን ደምፀ፤ የእመቤታችንን የኪዳነ ምሕረት በዓል በማስመልከት በማሕበራዊ ድረ-ገጽ ያስተላለፉትን ትምህርት ከዚህ ቀጥሎ አቅርበንላችኋል፡፡

Sunday, February 11, 2018

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤16 ክፍል ሰላሳ ስምንት

ከክፍል ሰላሳ ሰባት የቀጠለ፦
     የተወደዳችሁ አንባብያን! እንኳን የካቲት አምስት ቀን 2010 ዓ.ም ለምንጀምረው ዐቢይ ጾም  በሰላምና በጤና አደረሳችሁ አደረሰን፡፡
     ከዚህ በመቀጠል ስለ ዐቢይ ጾም መጠነኛ ግንዛቤ የምናገኝበት ትምህርት፤እንዲሁም በዐቢይ ጾም ውስጥ በሚውሉት ስምንት ሰንበታት  /እሑዶች/ በቅዳሴ ጊዜ የሚነበቡትን ምንባባት በተመለከተ በዝርዝር አቅርበንላችኋልና በጥሞና እንድትከታተሉት እንጋብዛለን፡፡

Wednesday, January 17, 2018

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤16 ክፍል ሰላሳ ሰባት

ከክፍል ሰላሳ ስድስት የቀጠለ፦

የተወደዳችሁ አንባብያን! እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደቱና የጥምቀቱ መታሰቢያ በዓላት በሰላምና በጤና አደረሳችሁ አደረሰን፡፡
     ሁላችንም የኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታዮች እንደምናውቀው፤ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ፤ ንጽሕት ቅድስት ከምትሆን ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ፤በዚህ ዓለም በቆየባቸው ሰላሳ ሶስት ዘመናት ማለትም በመዋዕለ ሥጋዌው የፈጸማቸው ሥራዎች በሁለት ዐበይት ክፍሎች ይከፈላሉ፡፡አንዱና ዋነኛው አዳምና ልጆቹ የተያዙበትን የበደል ዕዳ ዋጋ ከፍሎ /ቤዛ ሆኖ/ ነጻ ለማውጣት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ለአብነት /ለአርአያነት/ ነው፡፡በቤዛነት ሥራው የሰው ልጅ ሊሳተፍበት ስለማይችል እሱ ብቻ የፈጸማቸው ናቸው፡፡ከነዚህ ውስጥ ከእመቤታችን በድንግልና መወለዱ፣ በዮርዳኖስ ወንዝ ሲጠመቅ በዚያ ተቀብሮ የነበረውን የዕዳ ደብዳቤያችንን መደምሰሱ፣ በመጨረሻም በጽንስ የጀመረውን የቤዛነት ሥራ በመስቀል ላይ በመፈጸም የከፈለው ካሳ የሚጠቀሱት ናቸው፡፡በሌላ በኩል እሱ ጾሞ እንድንጾም፣እሱ ጸልዮ እንድንጸልይ፣እሱ ሰግዶ እንድንሰግድ፣ እሱ ለችግረኞችና ለበሽተኞች እንደ አዘነላቸውና እንደረዳቸው እኛም እንዲሁ እንድናደርግ፤ በአጠቃላይ ተከተሉኝ ባለን መንገድ ሁሉ እንድንከተለው፤በአምላካዊ ቃሉ እንዲህ ሲል አስተምሮናል፤"….ብትወዱኝ ትእዛዜን ጠብቁ…..! /ዮሐ.14፥15/ "....እርስ በርሳችሁ ትዋደዱ ዘንድ ትእዛዜ ይህች ናት…..."!  / ዮሐ.15፥12/፡፡አኛም የእግዚአብሔር የጸጋ ልጆች እስከሆንን ድረስ ትእዛዙን መፈጸም ይገባናል፡፡
     የተወደዳችሁ አንባብያን! የጌታችንን የልደቱን መታሰቢያ በዓል ታሕሳስ ሃያ ዘጠኝ ቀን አክብረን የጥምቀቱን በዓል ለማክበር እየተዘጋጀን ባለንበት ሰዓት፤ሁለቱንም በዓላት በማስመልከት ከማሕበራዊ ድረ-ገጽ ያገኘነውንና ለብዙዎቻችን ጥያቄ መልስ የሚሰጡንን ትምህርቶች ልናካፍላችሁ ወደድን፡፡ልደቱን በተመለከተ "Ydidya Mesgana"የተባሉ፤ ጥምቀቱን በተመለከተ ደግሞ "ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን ደምፀ" የተባሉት መምህር የሰጡትን ትምህርት፤ ጸሁፉን ለንባብ እንዲመች ከማስተካከል በስተቀር በሃሳቡ ላይ ምንም ሳንጨምርና ሳንቀንስ አቅርበንላችኋል፡፡

መልካም ንባብ! መልካም በዓል!

Friday, November 17, 2017

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤16 ክፍል ሰላሳ ስድስት

ከክፍል ሰላሳ አምስት የቀጠለ፦
የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? 
ለዚህ ዕለት ያደረሰን ልዑል እግዚአብሔር ስሙ ይመስገን፡፡
       የተከበራችሁ የዚች የጡመራ መድረክ ተከታታዮች፤ በክፍል ሰላሳ አምስት እራሳቸውን ‹‹ተሐድሶ ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ›› ብለው የሚጠሩት አጽራረ ቤተ ክርስቲያን፤ እውነተኛ የተዋሕዶ አማኝ መስሎ ለመታየት የሚጠቀሙባቸውን ዋና ዋና የማሳሳቻ ስልቶች ማሳየታችን ይታወሳል፡፡በዚህ ክፍል ደግሞ የዘመነ ጽጌን ፍጻሜ ምክንያት በማድረግ ጥቂት ትምህርታዊ መልእክት አለችን፡፡

መልካም ንባብ!

Tuesday, November 14, 2017

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤16 ክፍል ሰላሳ አምስት

ከክፍል ሰላሳ አራት የቀጠለ፦
የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? 
ለዚህ ዕለት ያደረሰን ልዑል እግዚአብሔር ስሙ ይመስገን፡፡
       የተከበራችሁ የዚች የጡመራ መድረክ ተከታታዮች፤ በክፍል ሰላሳ አራት እራሳቸውን ‹‹ተሐድሶ ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ›› ብለው የሚጠሩት አጽራረ ቤተ ክርስቲያን፤ እውነተኛ የተዋሕዶ አማኝ መስሎ ለመታየት የሚጠቀሙባቸውን የማሳሳቻ ስልቶች ለማሳየት መግቢያውን ጀምረን  በይቀጥላል ባቆየነውን መሠረት፤ እነሆ በዚህ ክፍል ዋና ዋናዎቹን ለማሳየት እንሞክራለን፡፡
መልካም ንባብ!

Saturday, September 23, 2017

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤16 ክፍል ሰላሳ አራት

ከክፍል ሰላሳ ሦስት የቀጠለ፦
የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? 
ለዚህ ዕለት ያደረሰን ልዑል እግዚአብሔር ስሙ ይመስገን፡፡

       የተከበራችሁ የዚች የጡመራ መድረክ ተከታታዮች፤ በክፍል ሰላሳ ሦስት "በቀጣይ ጽሁፋችን እራሳቸውን ‹‹ተሐድሶ ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ›› ብለው የሚጠሩት አጽራረ ቤተ ክርስቲያን፤ እውነተኛ የተዋሕዶ አማኝ መስሎ ለመታየት የሚጠቀሙባቸውን የማሳሳቻ ስልቶች በመጠኑ እንዳስሳለን" ብለን በይደር ባቆየነውን መሠረት፤ እነሆ በዚህ ክፍል ዋና ዋናዎቹን ለማሳየት እንሞክራለን፡፡
መልካም ንባብ!

Saturday, August 19, 2017

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤16 ክፍል ሰላሳ ሦስት

ከክፍል ሰላሳ ሁለት የቀጠለ፦
የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ?  
ለዚህ ዕለት ያደረሰን ልዑል እግዚአብሔር ስሙ ይመስገን፡፡
     የተከበራችሁ አንባብያን በክፍል ሰላሳ ሁለት  "በቀጣይ ጽሁፋችን እነዚሁ አጽራረ ቤተ ክርስቲያን / ተሐድሶ ተብዬዎቹ/ እውነተኛ መስሎ ለማሳሳት የሚጠቀሙባቸውን ዋና ዋና ስልቶች በመጠኑ እንዳስሳለን፡፡ "ብለን በይደር አቆይተነው እንደነበር ይታወሳል፡፡አሁንም ይህ የቤት ሥራችን እንዳለ ሆኖ ለዛሬው "አዘክሪ ድንግል"በሚል ርዕስ እመቤታችንን የምንማጸንበት ወቅታዊ መልእክት  አቅርበንላችኋል፡፡
መልካም በዓል፡፡