Saturday, May 21, 2016

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤16 ክፍል ሃያ

የተወደዳችሁ አንባብያን!
እንደምን ሰነበታችሁ ?
በክፍል አስራ ዘጠኝ ጽሁፋችን "ተሐድሶ ዘኦርቶዶክስ የእምነት መግለጫ" በመጽሐፍ ቅዱስ ሲመዘን! በሚል ርዕስ ጀምረን በይቀጥላል እንዳቆየነው ይታወሳል፡፡ ክፉውን ነገር እንድንጸየፍ ከበጎ ነገር ጋር እንድንተባበር ከቅዱሳት መጻሕፍት በተማርነው መሠረት ‹‹ቲጂ የተዋህዶ ልጅ ተዋህዶ››የተባለች እህታችን በface book ያስተላለፈችው ትምህርት የእኛም መልእክት ስለሆነ ሳንጨምርና ሳንቀንስ እንድታነቡት እንጋብዛለን፡፡

Sunday, May 1, 2016

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤16 ክፍል አስራ ዘጠኝ

   “ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡ማቴ.716 ክፍል አስራ ዘጠኝ
 "ተሐድሶ ዘኦርቶዶክስ የእምነት መግለጫ" በመጽሐፍ ቅዱስ ሲመዘን!
ከክፍል አስራ ስምንት የቀጠለ
የተወደዳችሁ አንባብያን!
እንደምን ሰነበታችሁ ?
‹‹ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ›› በሚለው ዐቢይ ርዕስ ሥር ከክፍል አንድ እስከ ዘጠኝ ባስነበብነው ጽሁፍ፤የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያናችን ትልቅ ፈተና የሆኑትን እራሳቸውን ‹‹ተሐድሶ ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ››ብለው የሚጠሩትን የበግ ለምድ የለበሱ ተኩላዎችን የጥፋት ተልእኮ ለማሳየት ሞክረናል፡፡የእኩይ ሥራቸው መራራ ፍሬዎች ከሆኑት መጻሕፍቶቻቸውም መካከል ‹‹የአዲሰ ኪዳን መካከለኛ» የተባለው መጽሐፍ በመጽሐፍ ቅዱስ ሲመዘን ቀሎ የተገኘ /ከፍሬው ገለባ/ መሆኑንም መጽሐፍ ቅዱስን ምስክር አድርገን አሳይተናል፡፡እንዲሁም

Friday, April 29, 2016

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤15 ክፍል አስራ ስምንት

ከክፍል አስራ ሰባት የቀጠለ

የተከበራቸሁ አንባብያን!
     በዚህ የመወያያ መድረክ (ወልድ ዋሕድ) ክፍል ስድስትና ሰባት ቤተ ክርስቲያናችን በመዝሙር በኩል እየገጠማት ያለውን ፈተና በማስመልከት ባቀረብነው ጽሁፍ መጠነኛ ግንዛቤ እንዳገኛችሁ እናምናለን፡፡እንዲሁም በክፍል አስራ ስድስትና አስራ ሰባት ደግሞ "Bini Zelideta" ከተባሉ ወንድማችን ከፌስ ቡክ ገጻቸው ላይ ያገኘነውን ጽሁፍ የእኛም ሃሳብ ስለሆነና ትልቅ መልእክት የሚያስተላልፍ ሆኖ ስላገኘነው ምንም ሳንጨምርና ሳንቀንስ አስነብበናችኋል፡፡አሁንም ከዚህ በመቀጠል "Blni Zelideta" መዝሙርን በተመለከተ የጻፉትን ክፍል ሦስትና ማጠቃለያውን እንድታነቡ እየጋበዝን፤ጉዳዩ ይመለከተናል የምንል ሁላችንም በዚህ ጽሁፍ ላይ በምናገኘው መልእክት መሠረት ችግሩን ከማስወገድ አኳያ የየድርሻችንን መልካም ስራ እንድናበረክት ለማሳሰብ እንወዳለን፡፡
መልካም ንባብ!

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤15 ክፍል አስራ ሰባት

ከክፍል አስራ ስድስት የቀጠለ

የተከበራቸሁ አንባብያን!
በዚህ የመወያያ መድረክ (ወልድ ዋሕድ) ክፍል ስድስትና ሰባት ቤተ ክርስቲያናችን በመዝሙር በኩል እየገጠማት ያለውን ፈተና በማስመልከት ባቀረብነው ጽሁፍ መጠነኛ ግንዛቤ እንዳገኛችሁ እናምናለን፡፡እንዲሁም በክፍል አስራ ስድስት ደግሞ "Bini Zelideta" ከተባሉ ወንድማችን ከፌስ ቡክ ገጻቸው ላይ ያገኘነውን ጽሁፍ ጥሩ አስተማሪ ሆኖ ስላገኘነው ምንም ሳንጨምርና ሳንቀንስ አስነብበናችኋል፡፡አሁንም ከዚህ በመቀጠል  ደግሞ የ"Blni Zelideta"ን ክፍል ሁለት መዝሙር ነክ ጽሁፍ አቅርበንላቸኋል!!!
መልካም ንባብ!

Sunday, March 27, 2016

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤15 ክፍል አስራ ስድስት

ከክፍል አስራ አምስት የቀጠለ
የተከበራቸሁ አንባብያን!
በዚህ የመወያያ መድረክ (ወልድ ዋሕድ) ክፍል ስድስትና ሰባት ቤተ ክርስቲያናችን በመዝሙር በኩል እየገጠማት ያለውን ፈተና በማስመልከት ባቀረብነው ጽሁፍ መጠነኛ ግንዛቤ እንዳገኛችሁ እናምናለን፡፡ከዚህ በመቀጠል ደግሞ "Bini Zelideta" ከተባሉ ወንድማችን ከፌስ ቡክ ገጻቸው ላይ ያገኘነውን ጽሁፍ አስተማሪ ሆኖ ስላገኘነው እንድታነቡት እንጋብዛለን፡፡
መልካም ንባብ!
Bini Zelideta
የተሃድሶ መናፍቃን መዝሙራት ሥውር ተልዕኮ!”
ክፍል-1 (ስለ ነገረ ክርስቶስ) /መልዕክቱ የረዘመው ግጥሞች ስለበዙበት ነው/
መግቢያ
ቅድስት፤ኦርቶዶክሳዊት ሃይማኖታችን ዕረፍት አልባ ዘመናትን ስታሳልፍ ዛሬ 2008 ዓመቷ ነው፡፡ ፈተናዎቿም እንደየ አዝማናቱና እንደፈታኞቿ የተለያዩ ነበሩ፡፡ ሠይፍ፣የዐላውያን መከራ፣የአናብሥት ትግል፣የክርስቲያኖች ስቃይ የሮም ኮሎሲየም አምፊ ቴአትር ትርዒት፣የቁም እሳት ቃጠሎ፣የካታኮምቡ ሕይወት፣የሠንሠለት ኑሮ እና የመንኩራኩር ስቃይ የመጀመሪያው እልህ አስጨራሽ ፈተናዋ ሲሆን እግር ተከትሎ፤ዓይነቱን ቀይሮ የመጣው የአርዮሳውያን ሃይማኖትን የመቀየር፣አስተምሕሮዋን የመበረዝ እንቅስቃሴ ጣሯን፣ሰቀቀኗን፣መከራዋን አብዝቶባት ቆይቷል፡፡ ዮዲት ጉዲት፣የካቶሊክ ሚሲዮናውያን፣ጽንፈኛ አሕዛቦችና የሉተር ርዝራዦች ዞረው ዞረው ሲሻቸው አንድ ላይ ሲሻቸው ደግሞ በፍርርቅ በመከረኛይቱ ሃይማኖት ላይ ቀንበር ሲጭኑ ኖረዋል ዛሬም ዕረፍት የላትም! የገሃነም ደጆች አይችሉአትም ተብሎ ስለተጻፈው አማናዊ ቃል ሁሉን አልፋ ዛሬ ብትደርስ ለሆዳቸው ያደሩ ሥጋውያን አስተምህሮዋን እናድሳለን ብለው ተነሡባት፡፡ ይህ ከቀደምት ዘመናት በዓይነትም በቅርጽም አካሄዱን ቀይሮ ቤተ ክርስቲያንን የማዳከም ሥልት ይዞ የተነሣው ፕሮቴስታንታዊ ቡድን ስውር ተልዕኮውን በቅድስት ቤተክርስቲያን ላይ በመሰንዘር ከፍተኛ ጥፋት አድርሷል አሁንም በማድረስ ላይ ይገኛል፡፡ የሃይማኖት ቅብ ይዘው፣ተቆርቋሪ መስለው መንገዷን ስታለች፣አስተምህሮዋ ልክ አይደለም፣አርጅታለች፣እናድሳታለን ባዮች ሲሆኑ በትምርቶቻቸው እና ከዘፈን በተቃኙ መዝሙሮቻቸው ትውልድን መበረዝ የዕለት እንጀራቸው አድርገውታል፡፡ በተለይም መዝሙሮቻቸው በአንድ ሌሊት ተደርሰው ንጋቱን ለጆሮ ስለሚበቁ ኑፋቄን ለማሰራጨት ደገኛ መሣሪያቸው ሆኖ በማገልገል ላይ ይገኛል፡፡

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤15 ክፍል አስራ አምስት

ከክፍል አስራ አራት የቀጠለ
"እያወቁ ማለቅ"
"ያላወቁ አለቁ ነበረ ተረቱ፤
እያወቁ ማለቅ መጣ በሰዓቱ፡፡"
     በሰማይም ሆነ በምድር ላይ ሁሉን ቻይ ከሆነው ከልዑል እግዚአብሔር እውቅና እና ፈቃድ ውጪ የሚከናወን ምንም ነገር እንደሌለ ይታወቃል፡፡ይታመናልም፡፡ይሁን እንጂ  ለስሙ ክብር ምስጋና ይግባውና አምላካችን እግዚአብሔር ሰውን ከሌሎች ፍጡራን ለይቶ በመልኩና በምሳሌው ሲፈጠረው የማሰብ፣የመናገርና ሕያው ሆኖ የመኖር ዕድል ሰጥቶታል፡፡የሰው ልጅ በዚህ በተሰጠው አእምሮ መመራት አቅቶት በኃጢአት ቢወድቅ፤ይህንን አድርግ ይህንን አታድርግ የሚል የተጻፈ ህግ /ህገ ኦሪትን/ ሰጠው፡፡በዚህ ብቻ አላበቃም፤እራሱ እግዚአብሔር ወልድ ወደዚች ምድር መጥቶ ለሰው ልጅ የቤዛነቱንና የአርአያነት ሥራውን ፈጸሞለታል፡፡ ጌታችን መድሐኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በጽንስ ጀምሮ በመሰቀል የፈጸመውን የቤዛነቱን ሥራ እፁብ! ድንቅ! ብሎ ከማመስገን በስተቀር በዚች አጭር ጽሁፍ የምንለው ነገር አይኖረንም፡፡በአርአያነት/በምሳሌነት/ ሥራው ግን ከኃጢአት በስተቀር የሰውን ህግ ሁሉ ፈጽሞ እኛም እንድንከተለው አዝዞናል፡፡በእኔ ያመነ እኔ የምሰራውን ሁሉ ያደርጋል፤እንደውም የበለጠ ያደርጋል ብሎ፡፡ዮሐ.14፥12፡፡

Sunday, March 6, 2016

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤15 ክፍል አስራ አራት

የተወደዳችሁ አንባብያን!
እንደምን ሰነበታችሁ ?
‹‹ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ›› በሚለው ዐቢይ ርዕስ ሥር፤ በክፍል አስራ አንድና አስራ ሁለት ላይ ወቅታዊ የሆነውን የኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን  የውስጥና የውጪ መናፍቃን/ተሐድሶዎች/ ችግር በማስመልከት ማህበረ ቅዱሳን በድረ-ገጹ (www.eotcmk.org) ያቀረበውን ዘገባ ተመልክታችሁ ጥሩ ግንዛቤ እንዳገኛችሁ በመገመት፤በመቀጠል ደግሞ "አምልኮተ ሰይጣን - ፍጻሜ “ተሐድሶ”?"
በሚለው ርዕስ ከማህበረ ቅዱሳን ድረ-ገጽ ያገኘነውን በማስረጃ የተደገፈ ዘገባ እነሆ ብለናል፡፡

መልካም ንባብ!