Wednesday, January 17, 2018

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤16 ክፍል ሰላሳ ሰባት

ከክፍል ሰላሳ ስድስት የቀጠለ፦

የተወደዳችሁ አንባብያን! እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደቱና የጥምቀቱ መታሰቢያ በዓላት በሰላምና በጤና አደረሳችሁ አደረሰን፡፡
     ሁላችንም የኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታዮች እንደምናውቀው፤ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ፤ ንጽሕት ቅድስት ከምትሆን ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ፤በዚህ ዓለም በቆየባቸው ሰላሳ ሶስት ዘመናት ማለትም በመዋዕለ ሥጋዌው የፈጸማቸው ሥራዎች በሁለት ዐበይት ክፍሎች ይከፈላሉ፡፡አንዱና ዋነኛው አዳምና ልጆቹ የተያዙበትን የበደል ዕዳ ዋጋ ከፍሎ /ቤዛ ሆኖ/ ነጻ ለማውጣት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ለአብነት /ለአርአያነት/ ነው፡፡በቤዛነት ሥራው የሰው ልጅ ሊሳተፍበት ስለማይችል እሱ ብቻ የፈጸማቸው ናቸው፡፡ከነዚህ ውስጥ ከእመቤታችን በድንግልና መወለዱ፣ በዮርዳኖስ ወንዝ ሲጠመቅ በዚያ ተቀብሮ የነበረውን የዕዳ ደብዳቤያችንን መደምሰሱ፣ በመጨረሻም በጽንስ የጀመረውን የቤዛነት ሥራ በመስቀል ላይ በመፈጸም የከፈለው ካሳ የሚጠቀሱት ናቸው፡፡በሌላ በኩል እሱ ጾሞ እንድንጾም፣እሱ ጸልዮ እንድንጸልይ፣እሱ ሰግዶ እንድንሰግድ፣ እሱ ለችግረኞችና ለበሽተኞች እንደ አዘነላቸውና እንደረዳቸው እኛም እንዲሁ እንድናደርግ፤ በአጠቃላይ ተከተሉኝ ባለን መንገድ ሁሉ እንድንከተለው፤በአምላካዊ ቃሉ እንዲህ ሲል አስተምሮናል፤"….ብትወዱኝ ትእዛዜን ጠብቁ…..! /ዮሐ.14፥15/ "....እርስ በርሳችሁ ትዋደዱ ዘንድ ትእዛዜ ይህች ናት…..."!  / ዮሐ.15፥12/፡፡አኛም የእግዚአብሔር የጸጋ ልጆች እስከሆንን ድረስ ትእዛዙን መፈጸም ይገባናል፡፡
     የተወደዳችሁ አንባብያን! የጌታችንን የልደቱን መታሰቢያ በዓል ታሕሳስ ሃያ ዘጠኝ ቀን አክብረን የጥምቀቱን በዓል ለማክበር እየተዘጋጀን ባለንበት ሰዓት፤ሁለቱንም በዓላት በማስመልከት ከማሕበራዊ ድረ-ገጽ ያገኘነውንና ለብዙዎቻችን ጥያቄ መልስ የሚሰጡንን ትምህርቶች ልናካፍላችሁ ወደድን፡፡ልደቱን በተመለከተ "Ydidya Mesgana"የተባሉ፤ ጥምቀቱን በተመለከተ ደግሞ "ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን ደምፀ" የተባሉት መምህር የሰጡትን ትምህርት፤ ጸሁፉን ለንባብ እንዲመች ከማስተካከል በስተቀር በሃሳቡ ላይ ምንም ሳንጨምርና ሳንቀንስ አቅርበንላችኋል፡፡

መልካም ንባብ! መልካም በዓል!

Friday, November 17, 2017

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤16 ክፍል ሰላሳ ስድስት

ከክፍል ሰላሳ አምስት የቀጠለ፦
የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? 
ለዚህ ዕለት ያደረሰን ልዑል እግዚአብሔር ስሙ ይመስገን፡፡
       የተከበራችሁ የዚች የጡመራ መድረክ ተከታታዮች፤ በክፍል ሰላሳ አምስት እራሳቸውን ‹‹ተሐድሶ ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ›› ብለው የሚጠሩት አጽራረ ቤተ ክርስቲያን፤ እውነተኛ የተዋሕዶ አማኝ መስሎ ለመታየት የሚጠቀሙባቸውን ዋና ዋና የማሳሳቻ ስልቶች ማሳየታችን ይታወሳል፡፡በዚህ ክፍል ደግሞ የዘመነ ጽጌን ፍጻሜ ምክንያት በማድረግ ጥቂት ትምህርታዊ መልእክት አለችን፡፡

መልካም ንባብ!

Tuesday, November 14, 2017

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤16 ክፍል ሰላሳ አምስት

ከክፍል ሰላሳ አራት የቀጠለ፦
የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? 
ለዚህ ዕለት ያደረሰን ልዑል እግዚአብሔር ስሙ ይመስገን፡፡
       የተከበራችሁ የዚች የጡመራ መድረክ ተከታታዮች፤ በክፍል ሰላሳ አራት እራሳቸውን ‹‹ተሐድሶ ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ›› ብለው የሚጠሩት አጽራረ ቤተ ክርስቲያን፤ እውነተኛ የተዋሕዶ አማኝ መስሎ ለመታየት የሚጠቀሙባቸውን የማሳሳቻ ስልቶች ለማሳየት መግቢያውን ጀምረን  በይቀጥላል ባቆየነውን መሠረት፤ እነሆ በዚህ ክፍል ዋና ዋናዎቹን ለማሳየት እንሞክራለን፡፡
መልካም ንባብ!

Saturday, September 23, 2017

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤16 ክፍል ሰላሳ አራት

ከክፍል ሰላሳ ሦስት የቀጠለ፦
የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? 
ለዚህ ዕለት ያደረሰን ልዑል እግዚአብሔር ስሙ ይመስገን፡፡

       የተከበራችሁ የዚች የጡመራ መድረክ ተከታታዮች፤ በክፍል ሰላሳ ሦስት "በቀጣይ ጽሁፋችን እራሳቸውን ‹‹ተሐድሶ ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ›› ብለው የሚጠሩት አጽራረ ቤተ ክርስቲያን፤ እውነተኛ የተዋሕዶ አማኝ መስሎ ለመታየት የሚጠቀሙባቸውን የማሳሳቻ ስልቶች በመጠኑ እንዳስሳለን" ብለን በይደር ባቆየነውን መሠረት፤ እነሆ በዚህ ክፍል ዋና ዋናዎቹን ለማሳየት እንሞክራለን፡፡
መልካም ንባብ!

Saturday, August 19, 2017

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤16 ክፍል ሰላሳ ሦስት

ከክፍል ሰላሳ ሁለት የቀጠለ፦
የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ?  
ለዚህ ዕለት ያደረሰን ልዑል እግዚአብሔር ስሙ ይመስገን፡፡
     የተከበራችሁ አንባብያን በክፍል ሰላሳ ሁለት  "በቀጣይ ጽሁፋችን እነዚሁ አጽራረ ቤተ ክርስቲያን / ተሐድሶ ተብዬዎቹ/ እውነተኛ መስሎ ለማሳሳት የሚጠቀሙባቸውን ዋና ዋና ስልቶች በመጠኑ እንዳስሳለን፡፡ "ብለን በይደር አቆይተነው እንደነበር ይታወሳል፡፡አሁንም ይህ የቤት ሥራችን እንዳለ ሆኖ ለዛሬው "አዘክሪ ድንግል"በሚል ርዕስ እመቤታችንን የምንማጸንበት ወቅታዊ መልእክት  አቅርበንላችኋል፡፡
መልካም በዓል፡፡

Wednesday, August 9, 2017

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤16 ክፍል ሰላሳ ሁለት

ከክፍል ሰላሳ አንድ የቀጠለ፦

የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ?

ለዚህ ዕለት ያደረሰን ልዑል እግዚአብሔር ስሙ ይመስገን፡፡

"በምሳሌ አፌን እከፍታለሁ"ማቴ.13፥34

       ለስሙ ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ ዓለም የመጣበት አንዱና ዋነኛው ዓላማ የአዳምን ዘር ከወደቀበት ለማንሳት፣ ማለትም በኃጢአቱ ምክንያት ከተፈረደበት ሞት ለማዳን ስለሆነ፤ ማንም ፍጡር ሊሳተፍበት በማይችለው የቤዛነት ሥራው አዳምን ከነልጅ ልጆቹ ከሞት ወደ ሕይወት አሸጋግሮናል፡፡ መለኪያ ለሌለው ለዚህ ፍቅሩ ምስጋና ይግባውና፤ ሁለተኛው ዓላማ ደግሞ በአርአያነት ተግባሩ እኛም እንድንከተለው ምሳሌ ሆኖ ለማሳየት ነው፡፡

Tuesday, August 8, 2017

“ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ፡፡” ማቴ.7፤16 ክፍል ሰላሳ አንድ

ከክፍል ሰላሳ የቀጠለ፦

የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ?

ለዚህ ዕለት ያደረሰን ልዑል እግዚአብሔር ስሙ ይመስገን፡፡

      ሐዋርያው ቅ/ጳውሎስ በሮሜ መልእክቱ ምዕ.12 ቁጥር 9  “ክፉውን ነገር ተጸየፉት፤ከበጎ ነገር ጋር ተባበሩ” ብሎ ባስተማረን መሠረት፤ዓላማችን አንድ እስከሆነ ድረስ፤ የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ሃይማኖትና ሥርዓት ጠብቀው የሚያስተምሩትን የተለያዩ መምህራንን ትምህርቶች፤በዚች የመወያያ ጦማር ላይ እንድታነቡ ስናደርግ እንደነበረ እናስታውሳለን፡፡
     ዛሬ በዚች ክፍል የምናስነብባችሁ "ማቴዎስ ናታኒም" የተባሉ ወንድማችን በማህበራዊ ድረ-ገጽ ላይ "ነገረ ክርስቶስ በገድላት" በሚል ርዕስ ያስተላለፉትን ጠቃሚ ትምህርት ነው፡፡የመልእክቱ ይዘት  ለእኛ ለተዋሕዶ ልጆች ትምህርት፤ እንዲሁም ሳይገባቸውና ሳይገባቸው (" "ጠብቆ ይነበብ) ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ሃይማኖታችንን ለሚተቹ ደግሞ ምላሽ የሚሰጥ ስለሆነ ሁላችን አንብበን እንድንጠቀምበት ማስተዋሉን ያድለን፡፡
ጽሁፉን ለንባብ እንዲመች ከማድረግና አንዳንድ የፊደላት እርማት ከማድረግ በስተቀር የራሳችንን ሃሳብ አልጨመርንም፡፡